
አዲስ አበባ ፤ ሚያዚያ 14/2017 (ኢዜአ)፡- ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ) ለኢትዮጵያ እድገት እና ልማት የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል የድርጅቱ ማኔጂንግ ዳይሬክተር ክርስታሊና ጆርጂዬቫ ገለጹ።
የዓለም ባንክ ግሩፕ እና የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ) ዓመታዊ የፀደይ ወቅት ስብሰባ ትናንት በዋሺንግተን ዲሲ ተጀምሯል።
የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ) ማኔጂንግ ዳይሬክተር ክሪስታሊና ጂኦርጂዬቫ ከስብስባው ጎን ለጎን ከገንዘብ ሚኒስትር አቶ አሕመድ ሽዴ እና ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ አቶ ማሞ ምህረቱ ጋር ተወያይተዋል።
ማኔጂንግ ዳይሬክተሯ የኢትዮጵያን ሪፎርም አጀንዳ አስመልክቶ ውይይት ማድረጋቸውን በኤክስ ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ገልጸዋል።
አይኤምኤፍ የኢትዮጵያን እድገት እና ልማት ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆኑንም አመልክተዋል።
የዓለም ባንክ ግሩፕ እና የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ) ዓመታዊ የፀደይ ወቅት ስብሰባ እስከ ሚያዚያ 18 ቀን 2017 ዓ.ም ይቆያል።
አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...
Mar 27, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...
Mar 27, 2026
Jul 17, 2025
Apr 24, 2025