
አርባ ምንጭ፤ መጋቢት 27/2017(ኢዜአ)፦ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል "ኢትዮጵያ ታምርት እኛም እንሸምት" በሚል መሪ ሃሳብ አውደ ርዕይና ባዛር በአርባ ምንጭ ከተማ ዛሬ ተከፍቷል።
በአውደ ርዕዩና ባዛሩ ላይ ከ60 በላይ መካከለኛ፣ አነስተኛና ከፍተኛ ኢንዱስትሪዎች ምርቶቻቸውን አቅርበዋል።
የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ፣ የክልሉ ብሔረሰቦች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ አዳማ ትንጳዬ እና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ቦጋለ ቦሼ እና ሌሎች የክልሉ ከፍተኛ አመራር አባላት አውደ ርዕይና ባዛሩን ከፍተዋል።

ዓላማው የኢንዱስትሪ ዘርፍ ለሀገር ኢኮኖሚ ያለውን ሚና ለማላቅና ተኪ ምርቶች በጥራትና በስፋት እንዲመረቱ በማድረግ የውጭ ምንዛሬን ለማዳንና ለማስገኘት እንደሆነም ተመላክቷል።
በዛሬው ዕለት በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የመጡ ለውጦችና ቀጣይ አቅጣጫዎች ዙሪያ ውይይት እንደሚደረግም ከመርሃ ግብሩ መረዳት ተችሏል።
በመርሃ ግብሩ ላይ የፌዴራል፣ የክልል፣ የጋሞ ዞን እና የአርባ ምንጭ ከተማ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...
Mar 27, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...
Mar 27, 2026
Jul 17, 2025
Apr 24, 2025