
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 23/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት አዲሱ የዲጂታልና ኢመርጂንግ ቴክኖሎጂ ኢኒሼቲቭ የነቃ ተሳትፎ እንደምታደርግ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ(ዶ/ር) ገለጹ።
ሚኒስትሩ ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ረዳት ዋና ፀሐፊ እና የዲጂታልና ኢመርጂንግ ቴክኖሎጂ ልዩ መልዕክተኛ አማንዲፕ ሲንግ ጊል(ዶ /ር) ጋር ዛሬ በጽህፈት ቤታቸው ተወያይተዋል።
የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ረዳት ዋና ፀሐፊ እና የዲጂታልና ኢመርጂንግ ቴክኖሎጂ ልዩ መልዕክተኛ አማንዲፕ ሲንግ ጊል(ዶ /ር) ተመድ በዲጂታላይዜሽን እና በሰው ሰራሽ አስተውሎት ዙሪያ ባቋቋመው አዲስ ኢኒሼቲቭ ኢትዮጵያ አንድ አካል ሆና በንቃት እንድትሳተፍ ጥሪ አቅርበዋል።

ሚኒስትሩ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የዲጂታላይዜሽን አስፈላጊነት ለሀገር እድገት ሊጫወት የሚችለውን ቁልፍ ሚና ከግምት ውስጥ በማስገባት በቴክኖሎጂ ዙሪያ የሚሰሩ የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት እና መሰል ተቋማት አስቀድሞ እንዲቋቋሙ ማድረጋቸውን ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ የተመድ አዲሱ ኢኒሼቲቭ አካል መሆኗ ቁልፍ ተግባር እንደሆነ በመግለጽ በንቃት እንደምትሳተፍ አመልክተዋል።
አዲሱ የተመድ የዲጂታልና ኢመርጂንግ ቴክኖሎጂ ኢኒሼቲቭ በሰው ሰራሽ አስተውሎት ዙሪያ ወጥ የሆነ አስተዳደር ለማውጣትና የአቅም ግንባት ሥራዎችን ለመሥራት መቋቋሙን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...
Mar 27, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...
Mar 27, 2026
Jul 17, 2025
Apr 24, 2025