
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 8/2017(ኢዜአ)፦ በቻይና የኢትዮጵያ አምባሳደር ተፈራ ደርበው ከኒው ዴቨሎፕመንት ባንክ ፕሬዝዳንት ዲልማ ሩሴፍ ጋር ዛሬ በቻይና ሻንጋይ ከተማ ተወያይተዋል።
ውይይቱ ኢትዮጵያ የባንኩ አባል ለመሆን ያቀረበችው ጥያቄ ያለበት ደረጃ እና የሁለቱ ወገኖች የጋራ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ መሆኑን በቤጂንግ የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ ያመለክታል።
ኒው ዴቨሎፕመንት ባንክ (በቀድሞ አጠራሩ የብሪክስ ልማት ባንክ) በብሪክስ አባል ሀገራት እ.አ.አ በ2014 ተቋቁሞ ከአንድ ዓመት በኋላ በ2015 ወደ ስራ መግባቱ ይታወቃል።
ግዙፉ የባለብዝሃ ወገን የልማት ባንክ ስምንት አባል ሀገራት አሉት።
ብራዚል፣ ሩሲያ፣ ህንድ፣ ቻይና፣ ደቡብ አፍሪካ፣ ባንግላዴሽ፣ የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች እና ግብጽ የባንኩ አባል ሀገራት ናቸው።
አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...
Mar 27, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...
Mar 27, 2026
Jul 17, 2025
Apr 24, 2025