የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ልዩ ዘገባ

<p>ጨፌ ኦሮሚያ ወቅታዊ መረጃዎችን ጨምሮ ዘርፈ ብዙ አገልግሎት መስጠት የሚያስችል የሞባይል መተግበሪያ ይፋ አደረገ</p>

Feb 10, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- ጨፌ ኦሮሚያ ለአባላቱና ለህብረተሰቡ ወቅታዊ መረጃዎችን ጨምሮ ዘርፈ ብዙ አገልግሎት መስጠት የሚያስችል የሞባይል መተግበሪያ በይፋ አስጀምሯል።


መተግበሪያው ጨፌው ለአባላቱ ወቅታዊ መረጃዎችን ለመስጠት እንዲሁም በጊዜና በቦታ ያልተገደቡ መረጃዎችን ተደራሽ በማድረግ ዲሞክራሲያዊ ስርዓት እንዲጠናከር ትልቅ ፋይዳ ያለው መሆኑም ተጠቁሟል።


በማስጀመሪያ መርሐ ግብሩ ላይ የጨፌ ኦሮሚያ አፈ-ጉባኤ ሰዓዳ አብዱራህማን፣ የጨፌው አባላትን ጨምሮ ሌሎች እንግዶች ተገኝተዋል።

አፈ-ጉባኤዋ ሰዓዳ አብዱራህማን በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ የሞባይል መተግበሪያው የጨፌው አባላት የሕዝብ ውክልና ስራቸውን በቀላሉ እንዲወጡ ምቹ ሁኔታን የሚፈጥር መሆኑን ተናግረዋል።

የጨፌው አባላት የጉባኤ አጀንዳዎችን፣ በጨፌው የተላለፉ ውሳኔዎችን ብሎም የተለያዩ መረጃዎችን በጊዜ እና በቦታ ሳይገደቡ እንዲያገኙ የሚያስችል መሆኑንም ገልጸዋል።

በተጨማሪም ከሕብረተሰቡ የሚነሱ ጥያቄዎችን የሚመለከታቸው አካላት ምላሽ እንዲሰጡ የሚያስችል መሆኑንም ተናግረዋል።


የሞባይል መተግበሪያው የወረቀት አሰራሮችን የሚያስቀር እና ዲጂታል አሰራሮችን ከማስፋፋት አኳያ ትልቅ ሚና እንዳለውም ገልጸዋል።

መተግበሪያው በዋናነት አምስት ትልልቅ መነሻዎችን(menu) የያዘ ሲሆን ሕጎች፣ ቀን መቁጠሪያ፣ ወቅታዊ ዜናዎችን፣ የጨፌውን አባላት ስም ዝርዝር እና የቋሚ ኮሚቴ አባላትን እንዲሁም ሴቲንግ ያለው መሆኑም ተጠቁሟል።

ጨፌው የሞባይል መተግበሪያውን ከኔዘርላንድስ ኢንስቲትዩት ፎር መልቲፓርቲ ዲሞክራሲ ተቋም ጋር በመተባበር ያበለጸገ ሲሆን ከዛሬ ጀምሮ ስራ ላይ እንደሚውልም ተጠቁሟል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ቱሪዝም የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑን እያስመሰከረ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) 

‎አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 11/2018 (ኢዜአ)፡- ቱሪዝም የኢኮኖሚያችን አንዱ ምሰሶ እንደመሆኑ የሀገራዊ ዕድገታችንን የወደፊት አቅጣጫ እየቀረጸ ያለ ዘርፍ መሆኑ...

Apr 20, 2026

የኮደርስ ስልጠና ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

ጅማ፤ ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡- በጅማ የኮደርስ ስልጠና የወሰዱ የመንግሥት ሠራተኞች ቀልጣፋና ዘመናዊ የሕዝብ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እያገዛቸው መሆኑን...

Apr 14, 2026

በምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ ነው

አምቦ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የፍራፍሬ ልማትን የማስፋፋት ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።...

Mar 27, 2026

ወሳኝ ምዕራፍ ላይ የደረሰው የኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ ያቀረበችው እ.አ.አ 2003 ነበር። ኢትዮጵያ በወቅቱ ጥያቄውን ካቀረበች በ...

Mar 27, 2026