የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ለሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የአገልግሎት ጥራትና ተደራሽነት መጠናከር ጉልህ አስተዋፅኦ እያበረከተ ይገኛል

May 12, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 3/2018(ኢዜአ)፦ ሀገር በቀል የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ለሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የአገልግሎት ጥራትና ተደራሽነት መጠናከር ጉልህ አስተዋፅኦ እያበረከተ እንደሚገኝ የኩባንያው ዋና ሥራ አስፈፃሚ ዊም ቫንሄሌፑቴ ገለጹ።

ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ከመጋቢት 23 ቀን 2017 ዓ.ም እስከ መጋቢት 22 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ያለውን የሥራ አፈፃጸም አስመልክቶ ለመገናኛ ብዙኃን መግለጫ ሰጥቷል።

መግለጫውን የሰጡት የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ዊም ቫንሄሌፑቴ፤ ኢትዮጵያ በዓለም ላይ ፈጣን ዕድገት እያስመዘገቡ ካሉ ሀገራት መካከል አንዷ ናት ብለዋል።

ለዚህም ሀገር በቀል የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ መርሃ ግብሩ ዕድገትን በማፋጠን በኩል ከፍተኛ ሚና እየተወጣ መሆኑን ገልጸዋል።

በኢትዮጵያ ፈጣንና ጤናማ የኢኮኖሚ ዕድገት ውስጥ በኢንቨስትመንት መሳተፍ አስደሳች መሆኑን ጠቁመው፤ የማክሮ ኢኮኖሚ አመላካች አዎንታዊ ውጤቶች ኢንቨስትመንትን በማበረታታት ምቹ የልማት ምኅዳር መፍጠሩን ተናግረዋል።

በቴሌኮም ዘርፍም አበረታች የቁጥጥር ለውጦች መምጣታቸውን ገልጸው፤ ይህም የሳፋሪኮም ኢትዮጵያን የ90 ቀናት ንቁ ደንበኞች ቁጥር 13 ነጥብ 6 ሚሊየን ማድረስ ማስቻሉን አስረድተዋል።

ይህም ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ54 ነጥብ 2 በመቶ ዕድገት ማሳየቱን በመግለጽ።

የኤም-ፔሳ (M-PESA) ተጠቃሚዎች ቁጥር 5 ነጥብ 2 ሚሊየን መድረሱንና በመተግበሪያው የተደረገው የገንዘብ ዝውውርም 32 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር መድረሱን አብራርተዋል።

የሞባይል ዳታ አገልግሎት በዓመታዊ ገቢ ላይ ትልቁን ድርሻ በመያዝ ጠንካራ ዕድገት ማሳየቱንም ጨምረው ጠቁመዋል።

በተጠናቀቀው የ2026 በጀት ዓመት 15 ነጥብ 9 ቢሊየን ብር ገቢ ማግኘቱንና ይህም የ130 ነጥብ 9 በመቶ ዕድገት እንዳለው አመላክተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ ምቹ የኢንቨስትመንት አካባቢ መፍጠር ዋነኛው የትኩረት አቅጣጫ ነው

ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...

Apr 23, 2026

በድሬዳዋ አስተዳደር አምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረት አቅማቸው ጨምሯል

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...

Apr 17, 2026

የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቷል

ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...

Apr 1, 2026

የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር የልማት አጀንዳ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...

Mar 26, 2026