የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በኦሮሚያ ክልል የህዝቡን የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች የሚመልሱ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል

Apr 8, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ጅማ፤ መጋቢት 26/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ለህዝቡ የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ምላሽ የሚሰጡ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በብልፅግና ፓርቲ የክልሉ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ ነመራ ቡሊ ገለጹ።

በጅማ ዞን ኦሞ ናዳ ወረዳ አሰንዳቦ ከተማ፣ በወረዳ ደረጃ የመጀመሪያ የሆነውን መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ዛሬ በይፋ ተጀምሯል።


አቶ ነመራ ቡሊ በዕለቱ ባስተላለፉት መልዕክት፣ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በክልሉ በስፋት እየተተገበረ መሆኑንና የህዝቡን የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች በሂደት ለመመለስ እየተከናወነ ያለ ተግባር መሆኑን ገልጸዋል።


አገልግሎቱ ብልሹ አሰራሮችን ከማስቀረት ባለፈ፣ የህዝቡን ጥያቄዎች አንድ በአንድ እየመለስን ለመሆናችን ማሳያ ነው ያሉት ኃላፊው፣ ወደፊትም አገልግሎቱን በማዘመን ለበርካታ ዜጎች ተደራሽ ለማድረግ በትኩረት ይሰራል ብለዋል።


የጅማ ዞን አስተዳዳሪ ቲጃኒ ናስር በበኩላቸው፣ የዞኑ ነዋሪዎች በተደጋጋሚ የሚያነሷቸውን የልማትና የአገልግሎት አሰጣጥ ጥያቄዎችን ለመፍታት መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን በወረዳ ደረጃ እየተስፋፋ መሆኑን ገልጸዋል።


የአሰንዳቦ ከተማ አስተዳዳሪ ነዚፍ ሼህ ከማል በማዕከሉ 11 ተቋማት 52 ዓይነት አገልግሎቶች በ8 መስኮቶች እንደሚሰጥ ጠቅሰው ባለሙያዎች ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት ስልጠና ወስደው ወደ ስራ ገብተዋል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ ምቹ የኢንቨስትመንት አካባቢ መፍጠር ዋነኛው የትኩረት አቅጣጫ ነው

ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...

Apr 23, 2026

በድሬዳዋ አስተዳደር አምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረት አቅማቸው ጨምሯል

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...

Apr 17, 2026

የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቷል

ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...

Apr 1, 2026

የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር የልማት አጀንዳ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...

Mar 26, 2026