🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ብልፅግና ለማሳለጥ የዲጂታልና ቴክኖሎጂ ክህሎት ልማት ውጤታማነትን ማስፋት እንደሚገባ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ሃብት ልማት፣ ሥራ ስምሪትና የቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አስገነዘበ።
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን በ22ኛ መደበኛ ስብሰባው የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴርን የ2018 በጀት ዓመት የ9 ወራት ዕቅድ አፈፃፀም ገምግሟል።

የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) በዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርታቸው፤ ሳይንስ፣ ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን የአንገብጋቢ ችግሮች መፍቻ ቁልፍ መሳሪያ ነው ብለዋል።
የኢትዮጵያን የዲጂታል ልማት ለማሳለጥም የ10 ዓመት መሪ ዕቅድና ከዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ የቀጠለ የዲጂታል ኢትዮጵያ-2030 ስትራቴጂ በመቅረፅ ውጤታማ ሥራ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
በክህሎት ልማትና በስታርት አፕ፣ በሮቦቲክስና ሳይበር ደኅንነት፣ በስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል፣ በጥናትና ምርምር፣ በዲጂታል ግብይት፣ በጥናትና ምርምር ከፍተኛ ውጤት እየተገኘ መሆኑን ተናግረዋል።
በተለይም የመሶብ አንድ ማዕከል የዲጂታል አገልግሎት ለዜጎች የመንግስትን አገልግሎት በማሳለጥ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ እንደሚገኝ አንስተዋል።
የምክር ቤቱ አባላትም፤ በመንግሥት አገልግሎቶች፣ በሰው ሰራሽ አስተውሎት፣ የፈጠራ ውጤታማነትና ቀጣይ አቅጣጫን አስመልክቶ ጥያቄና አስተያየት አቅርበዋል።
የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር)፤ በሰጡት ምላሽና ማብራሪያ የቴክኖሎጂ ዕውቀት ለማሳደግ ተቋማትን የሚደግፍ ካውንስል ተዋቅሮ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ በሀገሪቱ ጠረፋማ አካባቢዎች የሃይል እና የኢንተርኔት ተደራሽነትን ለማረጋገጥ ተቋሙ ራዕይ አንግቦ እየሰራ እንደሆነም ገልጸዋል።
በቀጣይም የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ የዲጂታል ሽግግር ለማፋጠን የተፈጠረውን አስቻይ የፈጠራና ክህሎት ልማት ምኅዳር የበለጠ በማጠናከር ውጤታማ ሥራ እንደሚሰራ ተናግረዋል።

በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ሃብት ልማት፣ ሥራ ስምሪትና የቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ነገሪ ሌንጮ (ዶ/ር)፤ የዲጂታል ልማት የኢኮኖሚ ዕድገት ማሳለጫ መሳሪያ ነው ብለዋል።
የኢትዮጵያን የዲጂታል ልማትና ሽግግር ለማፋጠን የተዘረጉ አስቻይ የአሰራር ምኅዳሮችም ውጤት በማምጣት የዜጎችን ተጠቃሚነት እያረጋገጡ እንደሚገኙ ገልጸዋል።
በተለይም የኢትዮ-ኮደርስ ስልጠና የዜጎችን የፈጠራ ክህሎትና ዕውቀት በማበልፀግ አይነተኛ ሚና እየተወጣ እንደሚገኝ አንሰተዋል።
በቀጣይም የኢትዮጵያን የዲጂታል ሉዓላዊነት በማረጋገጥ ሁለንተናዊ ብልፅግናን የሚያረጋግጥ የፈጠራና ክህሎት ልማት ሥራዎች የበለጠ ሊጠናከሩ እንደሚገባ አሳስበዋል።
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...
May 20, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...
May 7, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...
May 7, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026