የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

በኮምቦልቻ ከተማ የተገነቡ የምግብ ዘይት እና የቆርቆሮ ማምረቻ ፋብሪካዎች ተመርቀው ስራ ጀመሩ

May 12, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ኮምቦልቻ፤ ግንቦት 4/2018(ኢዜአ)፡-በኮምቦልቻ ከተማ ከ877 ሚሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ የተገነቡ የምግብ ዘይት እና የቆርቆሮ ማምረቻ ፋብሪካዎች ተመርቀው ሥራ ጀመሩ።

በምረቃ ሥነ-ስርዓቱ የአማራ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ፋንቱ ተስፋዬ፣ የክልሉ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ኃላፊ እንድሪስ አብዱ እና ሌሎችም የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።

የኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ ኃላፊ አቶ ሁሴን ሙሄ እንደገለፁት፣ በከተማው የኢንዲስትሪ ዘርፉን ለማሳደግ በልዩ ትኩረት እየተሰራ ይገኛል።

ባለፉት ጥቂት ወራትም ስድስት ኢንዱስትሪዎች ወደ ማምረት የገቡ ሲሆን ፤ዛሬ የተመረቁትን ጨምሮ አጠቃላይ 69 አምራች ኢንዱስትሪዎች እንዳሉም ገልፀዋል።

ኢንዱስትሪዎቹ ወደ ሃገር ውስጥ የሚገቡ ምርቶችን በመተካትና ለውጭ ገበያ የሚቀርቡ ምርቶችን በማምረት ኢኮኖሚው እንዲነቃቃ እያገዙ ነው ብለዋል።


በዛሬ እለት ተመርቀው ወደ ማምረት የተሸጋገሩት የምግብ ዘይትና ቆርቆር ማምረቻ ፋብሪካዎችም ለአካባቢው ተጨማሪ አቅም የሚፈጥሩ ናቸው ሲሉ ገልፀዋል።

የኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ መሀመድአሚን የሱፍ በበኩላቸው፤ የኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ዘርፉ ለከተማዋ ፈጣን እድገት የበኩሉን አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው ብለዋል።

የከተማዋ ለወደብ ቅርብ መሆን፣ የአየር ትራንስፖርት መኖር፣ አስተማማኝ ሰላም መረጋገጡና ሌሎችም ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን ገልፀዋል።

በአሁኑ ወቅትም ዘርፉን ለማሳደግ በተቀናጀ አግባብ በተደረገ ድጋፍና ክትትል ውጤት ማስመዝገብ መቻሉን ነው ያስገነዘቡት።

የ"ሁዳ" ምግብ ዘይት ፋብሪካ ባለቤት ተወካይ አቶ ሀሰን ሰይድ በበኩላቸው፣ በ127 ሚሊዮን ብር ወጪ የተገነባው ፋብሪካው በቀን 50 ሺህ ሊትር ዘይት የማምረት አቅም እንዳለው ተናግረዋል።


መንግስት ለግል ባለሃብቶችና ለዘርፉ የሰጠው ትኩረት ውጤታማ እንዳደረጋቸው አንስተው፤ ፋብሪካው ከ250 ለሚበልጡ ዜጎችም የስራ እድል ይፈጥራል ብለዋል።

ሌላው "የኡሙል ኸይር" ቆርቆሮ ፋብሪካ ባለቤት አቶ መሀመድ አብደላ በበኩላቸው፤ ከ750 ሚሊዮን ብር በሚበልጥ ወጭ የተገነባው ፋብሪካው በቀን ከ21 ሺህ በላይ ቆርቆሮ እያመረተ ነው ብለዋል።

ፋብሪካው በሙሉ አቅሙ ወደ ስራ ሲገባም በቀን 40 ሺህ ቆርቆሮ የማምረት አቅም እንዳለውም ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢንዱስትሪ ፓርኩ መገንባት መንግሥት ለዘርፉ የሰጠውን ትኩረት በተጨባጭ ያረጋገጠ ነው

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...

May 20, 2026

የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል 

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...

May 7, 2026

የከተማዋን ባህል፣ ታሪክ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በማልማት ለኢኮኖሚያዊ ጥቅም የማዋል ተግባራት ይጠናከራሉ

ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...

May 7, 2026

ከአፍሪካ አቪዬሽን መሪነት እስከ አህጉራዊ የኢኮኖሚ ትስስር

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...

Apr 24, 2026