የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

በኢትዮጵያ የብድር አስተዳደር ላይ በተከናወኑ ውጤታማ ሥራዎች በዕዳ ዕፎይታ ተጨባጭ ለውጥ ተመዝግቧል

May 7, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦በኢትዮጵያ የብድር አስተዳደር ላይ በተከናወኑ ውጤታማ ሥራዎች በዕዳ ዕፎይታ ተጨባጭ ለውጥ መመዝገቡን የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ሰመሪታ ሰዋሰው ገለጹ፡፡

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ያዘጋጀው ዛሬን ጨምሮ ለሶስት ቀናት የሚካሄደው ሁለተኛው የአፍሪካ ሉዓላዊ ፋይናንስ ፎረም እየተካሄደ ይገኛል፡፡

በፎረሙ መክፈቻ ላይ የገንዘብ ሚንስትር ዴኤታ ሰመሪታ ሰዋሰው እንደተናገሩት፤ የብድር ዕዳ አስተዳደር ለማክሮ ኢኮኖሚ መረጋጋት፣ ለልማት ስትራቴጂና ለፖሊሲ ተዓማኒነት መሰረት ነው።

በኢትዮጵያ ዕዳ አስተዳደር ላይ በተከናወኑ ወጤታማ ስራዎች የብድር ዕፎይታ ላይ ተጨባጭ ለውጥ መመዝገቡን ገልጸዋል።

ኢትዮጵያ በቡድን-20 የጋራ ማዕቀፍ ስር ትልቅ ምዕራፍ ላይ መድረሷን ገልጸው፤ ከ3 ነጥብ 5 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር በላይ የብድር እፎይታ ጊዜ አግኝታለች ብለዋል።

በኢትዮጵያ ማክሮ ኢኮኖሚ መረጋጋትን ለመፍጠር ሁሉን አቀፍ ሪፎርም በማካሄድ ወደ ገበያ መር የውጭ ምንዛሬ ሥርዓት መሸጋገር፣ የገንዘብ ፖሊሲን ማጠናከር፣ የሀገር ውስጥ ገቢ አሰባሰብን ማሳደግ፣ በዕዳ አስተዳደር ግልጽነትን መፍጠር እንዳስቻለ ገልጸዋል፡፡

በዚህም የዋጋ ግሽበትን መቀነስ፣ የወጭ ንግድ ገቢን ማሳደግ እና የውጭ ምንዛሬ ክምችትን በማሳደግ ጠንካራ ኢኮኖሚ መገንባት ተችሏል ብለዋል፡፡

በመካከለኛው ምስራቅ ውጥረት የነዳጅ ዋጋ እንዲጨምር እና የንግድ መስመሮች እንዲስተጓጎሉ ማድረጉን ጠቅሰው፤ በአፍሪካ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ ማሳደሩን ገልጸዋል፡፡

በመሆኑም በአፍሪካ ዘላቂነት ያለው ኢኮኖሚ ለመገንባት ​የብድር ወጪን መቀነስ፣ የሀገር ውስጥ እና ቀጣናዊ የፋይናንስ ገበያዎችን እና ​የዕዳ አስተዳደር አቅምን ማጠናከር ይገባል ብለዋል፡፡

የውጭ ፋይናንስ ጥገኝነትን ለመቀነስ የሀገር ውስጥ የምንዛሪ ቦንድ ገቢን ማሳደግ ይገባል ያሉት ሚኒስትር ዴኤታዋ፤ ብድር የልማት እንቅፋት ሳይሆን የልማት መሣሪያ የሚሆኑበትን አሰራር ማስፈን እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡


በተባበሩት መንግሥታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ዋና ፀኃፊ ክላቨር ጋቴቴ በበኩላቸው፤ ዓለም አቀፋዊ የጅኦፖለቲካ ውጥረቶች የአፍሪካን የጸጥታና የንግድ ፍሰት በማስተጓጎል የሸቀጦችን ዋጋ አንሯል ብለዋል፡፡

ይሄውም የኢንቨስትመንት ፍላጎትን በመገደብና የካፒታል ዋጋን በመጨመር የአፍሪካን የኢንቨስትመንት ተመራጭነት ገድቧል ብለዋል፡፡

የዕዳ ስልቶችን ከአየር ንብረት እና ከልማት ግቦች ጋር ማጣጣም ፣ ​ተቋማዊና የመረጃ ምንጮችን ማጠናከር፣ የተቀናጀ የፋይናንስ ስርዓት መዘርጋት አስፈላጊ መሆኑን አስረድተዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢንዱስትሪ ፓርኩ መገንባት መንግሥት ለዘርፉ የሰጠውን ትኩረት በተጨባጭ ያረጋገጠ ነው

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...

May 20, 2026

የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል 

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...

May 7, 2026

የከተማዋን ባህል፣ ታሪክ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በማልማት ለኢኮኖሚያዊ ጥቅም የማዋል ተግባራት ይጠናከራሉ

ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...

May 7, 2026

ከአፍሪካ አቪዬሽን መሪነት እስከ አህጉራዊ የኢኮኖሚ ትስስር

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...

Apr 24, 2026