የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

የመስሪያ ቦታና የመሰረተ ልማት አቅርቦት መኖሩ በተሰማራንበት ዘርፍ ውጤታማ አድርጎናል- አምራች ኢንዱስትሪዎች

Apr 29, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሀዋሳ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦መንግስት ባደረገላቸው የመስሪያ ቦታና የተሳለጠ የመሰረተ ልማት አቅርቦት በተሰማሩበት መስክ ውጤታማ መሆናቸውን አምራች ኢንዱስትሪዎች ገለጹ፡፡

ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከ350 ሚሊዮን ዶላር በላይ ተኪና የወጪ ምርት በክልሉ በሚገኙ አምራች ኢንዱስትሪዎች በኩል መመረቱን የክልሉ ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ገልጿል፡፡

የአምራች ኢንዱስትሪዎቹ የስራ ኃላፊዎች ለኢዜአ እንደገለፁት፤ መንግስት የመስሪያ ቦታና የተሳለጠ የመሰረተ ልማት አቅርቦት እንዲኖር ማድረጉ በተሰማሩበት ዘርፍ ውጤታማ እንዲሆኑ እያደረገ ነው።

በሀዋሳ ከተማ በፎምና በቴራዞ ምርት የተሰማሩት አምራች ኢንዱስትሪ ስራ አስኪያጆች አቶ ዘሪሁን ሀይለማሪያም እና አቶ አዲስ አበበ፤ መንግስት የመስሪያ ቦታ፣የኃይልና ሌሎች አቅርቦቶች በማመቻቸቱ በአጭር ጊዜ ውጤታማ እንደሆኑ ገልጸዋል፡፡

በአንድ ላይ 230 ለሚሆኑ ዜጎች የስራ ዕድል እንደፈጠሩ የሚገልጹት አምራች ኢንዱስትሪዎቹ ከውጭ የሚገባውን ምርት በመተካት ረገድ ውጤታማ ስራ እየሰሩ መሆኑን አመልክተዋል።

የኩል ፕላስቲክ ሪሳይክሊንግ ኢንተርፕራይዝ ሥራ አስኪያጅ ወይዘሮ ሰላማዊት ቶማስ በበኩላቸው፤ መንግስት እያደረገ ያለው ድጋፍ ተኪ ምርት በማምረት ስኬታማ እንዲሆኑ ማድረጉን አስረድተዋል፡፡

በአምራች ኢንዱስትሪዎቹ የሥራ ዕድል ከተፈጠረላቸው ዜጎች መካከል ወጣት ሰለሞን ጋሻው በተፈጠረለት የስራ ዕድል ቤተሰቡን እያስተዳደረ እንደሚገኝ ነው የገለጸው።

ባገኘው የስራ ዕድልም ከሚያገኘው ገቢ በተጨማሪ የዕውቀት ሽግግር ዕድል ማግኘቱንም ተናግሯል።

የሲዳማ ክልል የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ አሻግሬ ጀንበሬ ለኢዜአ እንደገለጹት ፤በክልሉ በወጪና ተኪ ምርቶች ላይ የተሰማሩ አምራች ኢንዱስትሪዎች የማምረት አቅምን ለማጎልበት የሚያስችሉ ስራዎች በተቀናጀ መንገድ እየተከናወኑ ነው፡፡

በተለይም የኤሌክትሪክ ኃይል፣ ጥሬ ዕቃ፣ የተማረ የሰው ኃይልና ሌሎች አቅርቦቶችን በማመቻቸትና በምርታማነት ሂደት የሚያጋጥሙ ተግዳሮቶችን ለቅሞ ለመፍታት የተወሰዱ እርምጃዎች ውጤት ማምጣታቸውን ጠቅሰዋል፡፡

በዚህም በክልሉ የኢንዱስትሪዎች የማምረት አቅም ከ65 በመቶ በላይ ዕድገት ማሳየቱን ጠቁመው ባለፉት ዘጠኝ ወራት ወደ ውጭ ከተላኩ ምርቶች ከ120 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ተገኝቷል ነው ያሉት።

በዚህም ከ230 ሚሊዮን ዶላር በላይ የሚያወጣ ምርት መተካት መቻሉን ተናግረዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢንዱስትሪ ፓርኩ መገንባት መንግሥት ለዘርፉ የሰጠውን ትኩረት በተጨባጭ ያረጋገጠ ነው

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...

May 20, 2026

የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል 

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...

May 7, 2026

የከተማዋን ባህል፣ ታሪክ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በማልማት ለኢኮኖሚያዊ ጥቅም የማዋል ተግባራት ይጠናከራሉ

ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...

May 7, 2026

ከአፍሪካ አቪዬሽን መሪነት እስከ አህጉራዊ የኢኮኖሚ ትስስር

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...

Apr 24, 2026