🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡- የኦሮሞ ምርምር ማህበር የኦሮሞን ህዝብ ታሪክ ለመሰነድና ትውልድን በእውቀት ለመቅረጽ ልዩ ትኩረት መስጠቱን ገለጸ።
ማህበሩ ከአምቦ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር ያዘጋጀው 2ኛው ዓለም አቀፍ የምርምር ኮንፈረንስ መካሄድ ጀምሯል።

የማህበሩ የቦርድ ሰብሳቢ ፕሮፌሰር በቀለ ጉተማ፤ የኦሮሞ ምርምር ማህበር የኦሮሞን ህዝብ ታሪክ፣ ባህል፣ ቋንቋ እና የገዳ ስርዓትን በጥናትና ምርምር በመፈተሽ ለትውልድ ለማስተላለፍ በቁርጠኝነት እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
የኦሮሞን ጥልቅ ዕውቀት መመርመርና ማሳወቅ፣ የህዝቡን ትናንት አጥንቶ ማስገንዘብ፣ ዛሬን መፈተሽና መተቸት፣ እንዲሁም የወደፊቱን እጣ ፈንታ መተንበይና አቅጣጫ መጠቆም ከማህበሩ ተልዕኮዎች ዋነኞች መሆናቸውን ገልጸዋል።
በተጨማሪም ማህበሩ ትውልዱን በማስተማርና የወደፊት ጉዞውን ለማቅናት የተለያዩ ጥናታዊ ጽሁፎችንና መድረኮችን በማዘጋጀት፤ ባህልና እሴቶችን ለተተኪው ትውልድ ለማስተላለፍ ምሁራንን በማሳተፍ ላይ እንደሚገኝም ገልጸዋል።
ማህበሩ ከተመሰረተ ጀምሮ የተለያዩ ኮንፈረንሶችን በማዘጋጀት ምሁራን በኦሮሞ ጉዳዮች ላይ ሃሳብ እንዲለዋወጡ ማድረጉን ገልጸው፤ በአሁኑ ወቅትም በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ምርምር እያደረገ መሆኑን ጠቁመዋል።
በዚህም በባህላዊና ታሪካዊ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ አራት መጻህፍት በተለያዩ ቋንቋዎች አሳትሞ ማሰራጨቱን አስታውሰዋል።
በአሁኑ ወቅትም በስድስት የተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ምርምሮች እየተካሄዱ መሆኑንና በቅርቡ ለህትመት እንደሚበቁም ጠቁመዋል።

የአምቦ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት ሰለሞን ማሾ (ዶ/ር)፤ ዩኒቨርሲቲው በኦሮሞ ባህልና እሴቶች ላይ በንቃት እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
ከዚህም ባለፈ ዩኒቨርሲቲው በዘርፉ ከሚሰሩ ማናቸውም ተቋማት ጋር በቁርጠኝነት እየሰራ እንደሚገኝና ወደፊትም አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል።

በኮንፈረንሱ ላይ የተገኙት የቀድሞው የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ሙላቱ ተሾመ (ዶ/ር) በበኩላቸው፣ መሰል የምርምር ተቋማት የህዝብን ታሪክ፣ ባህልና ማንነት ጠብቆ ለትውልድ ለማስተላለፍ ያላቸው ፋይዳ የላቀ መሆኑን ገልጸዋል።
ለሁለት ቀናት በሚቆየው በዚህ ዓለም አቀፍ ጉባኤ ላይ የተለያዩ ጥናታዊ ጽሁፎች ቀርበው ሰፊ ውይይት ይደረግባቸዋል።
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...
May 20, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...
May 7, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...
May 7, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026