የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የባቡር ሐዲድ

ኢትዮጵያ እና ፈረንሳይ የኢኮኖሚ አጋርነታቸውን ያጠናክራሉ

Apr 21, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 13/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ፈረንሳይ በኢኮኖሚ ዘርፍ ላይ ያላቸውን አጋርነት ለማጠናከር ተስማምተዋል።

የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ የዓለም ባንክ እና የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) የፀደይ ስብሰባ ጎን ለጎን በዋሽንግተን ዲሲ ከፈረንሳይ ግምጃ ቤት ከፍተኛ ኃላፊዎች ጋር ተወያይተዋል።

ውይይቱ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የሁለትዮሽ የልማት ትብብር ይበልጥ ማሳደግ በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ ያተኮረ እንደነበርም ተመላክቷል።


ፈረንሳይ የመንግሥታት አበዳሪዎች ኮሚቴን በሊቀ መንበርነት በመራችበት ወቅት በኢትዮጵያ የዕዳ ሽግሽግ ሂደት ላይ ላበረከተችው አስተዋጽኦም ሚኒስትር አህመድ ሽዴ አመስግነዋል።

ሁለቱ ሀገራት በኢትዮጵያ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ እና በዕዳ መልሶ ማዋቀር ሂደት ላይ በጋራ ለመስራት ቁርጠኛ መሆናቸውንም አስታውቀዋል።

ይህም አዳዲስ የፋይናንስ ፍሰቶችን ለማምጣትና ዘላቂ የኢኮኖሚ ዕድገትን ለማረጋገጥ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው ኢዜአ ከገንዘብ ሚኒስቴር ያገኘው መረጃ ያመላክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የኢንዱስትሪ ፓርኩ መገንባት መንግሥት ለዘርፉ የሰጠውን ትኩረት በተጨባጭ ያረጋገጠ ነው

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...

May 20, 2026

የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል 

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...

May 7, 2026

የከተማዋን ባህል፣ ታሪክ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በማልማት ለኢኮኖሚያዊ ጥቅም የማዋል ተግባራት ይጠናከራሉ

ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...

May 7, 2026

ከአፍሪካ አቪዬሽን መሪነት እስከ አህጉራዊ የኢኮኖሚ ትስስር

በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...

Apr 24, 2026