🔇Unmute
ገንዳውኃ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦ በምዕራብ ጎንደር ዞን ገንዳውኃ ከተማ በህገ ወጥ መንገድ ተከማችቶ የነበረ ከ950 ሊትር በላይ ነዳጅ መያዙን የከተማ አስተዳደሩ ፖሊስ ጽህፈት ቤት አስታወቀ።
የከተማ አስተዳደሩ ፖሊስ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ኢንስፔክተር ሀይሌ ብርሃኑ 900 ሊትር ናፍጣ እና 56 ሊትር ቤንዚን በግለሰብ ቤት ከተደበቀበት ለመያዝ መቻሉን ገልጸዋል።

በህገ ወጥ መንገድ ተከማችቶ የነበረው ነዳጅ ሊያዝ የቻለው የጸጥታ አካላት ባደረጉት ድንገተኛ ፍተሻና ጥብቅ ክትትል መሆኑንም ተናግረዋል።
እንደ ኃላፊው ገለጻ ነዳጁ በህገወጥ መንገድ ተከማችቶ የተገኘው በከተማው ቀበሌ 03 ልዩ ቦታው ቀጠና 08 በተባለ አካባቢ ነው።

በቀጣይም በሀገር ኢኮኖሚ ላይ ጫና የሚፈጥሩ መሰል ህገ ወጥ ተግባራትን ለመከላከል የቁጥጥር ሥራው ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።
ህብረተሰቡ ህገ ወጥ ተግባር ተፈጽሞ ሲያይ ለጸጥታ አካላት ፈጥኖ ጥቆማ በመስጠት እያደረገ ያለውን ትብብር በቀጣይም አጠናክሮ እንዲቀጥል ኃላፊው ጥሪ አቅርበዋል።
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...
May 20, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...
May 7, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...
May 7, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026