
አዲስ አበባ፤ የካቲት 19/2017(ኢዜአ)፡- የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት የሱፐርቪዥን ቡድን አባላት በኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት የስራ ምልከታ አድርገዋል፡፡
የሱፐርቪዥን ቡድኑ በተቋሙ የበለፀጉ የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ የቴክኖሎጂ ስራዎችን መገምገሙንና በኢንስቲትዩቱ የተለያዩ የስራ ክፍሎች ተዘዋውሮ መመልከቱን ከኢንስቲትዩቱ የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡

የኢንስቲትዩቱን ስራዎች በተመለከተ የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ወርቁ ጋቸና(ዶ/ር) ዝርዝር ማብራሪያ ማቅረባቸውም ተገልጿል፡፡
ኢንስቲትዩቱ ከዕድሜው በላይ የሆኑ ስራዎች መስራቱን የሱፐርቪዥን ቡድኑ መሪ ዶክተር ቀነዓ ያደታ አንስተው ተቋሙ ለሀገር ትልቅ አቅም እንደሆነ መጠቆማቸውም ተመላክቷል፡፡

ይህን አቅም በተለያዩ ዘርፎች ለሚታዩ ችግሮች መፍቻ ቁልፍ ለማድረግ ከሌሎች ተቋማት ጋር በቅርበት መስራት እንደሚያስፈልግ አጽንዖት ሰጥተው ተናግረዋል፡፡
በኢንስቲትዩቱ በበለፀጉ የቴክኖሎጂ ስራዎች የብዙኃንን ተጠቃሚነት ከማረጋገጥ አንጻር እንዲሁም ከሌሎች ተቋማት ጋር ኢንስቲትዩቱ በቅንጅት ስለሚሰራበት አግባብ በሱፐርቪዥን ቡድኑ አባላት ጥያቄዎች ቀርበው በዋና ዳይሬክተሩ ምላሽ እንደተሰጣቸውም ተገልጿል፡፡
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ መገንባት መንግሥት የኢንዱስትሪው ዘርፍ ለሀገር ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በፖሊሲና ...
May 20, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ውጤታማ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ...
May 7, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 28/2018 (ኢዜአ)፦ የደብረ ማርቆስ ከተማን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርስና ማህበራዊ እሴት በመጠበቅና በማልማት ለቱሪስት መስህብነት ለማዋ...
May 7, 2026
በሙሴ መለሰ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአቪዬሽን ታሪክ ታይቶ የማይታወቅና በአህጉሪቱ ትልቁ የሆነውን የ12 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ግዙፍ የኤርፖርት ግንባታ ፕሮጀክት...
Apr 24, 2026