የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ ለግብርና ቴክኖሎጂ ትኩረት ተሰጥቷል

May 20, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ታርጫ ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልልየግብርናውን ዘርፍ በምርምር በማስደገፍ የአርሶ አደሩን ሕይወት በመሠረታዊነት ለመቀየር የተጀመረው ሥራ ውጤታማ መሆኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) ገለጹ።

ርዕሰ መስተዳድሩ በ137 ሚሊዮን ብር የተገነባውን የታርጫ ግብርና ምርምር ማዕከል ሕንጻን መርቀው ለአገልግሎት ክፍት አድርገዋል።


በመርሐ ግብሩ መልዕክት ያስተላለፉት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)፣ በክልሉ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ ለግብርና ቴክኖሎጂና ምርታማነታቸው የተረጋገጡ ምርጥ ዘሮች ለአርሶ አደሩ ተደራሽ ተደርገዋል ብለዋል።

ዛሬ የተመረቀው የምርምር ማዕከልም የግብርናውን ዘርፍ በምርምር በማገዝ የአርሶ አደሩን ሕይወት በመሠረታዊነት ለመቀየር፣ አርሶ አደሩን የማሠልጠንና በምርምር የሚያወጣቸውን ምርጥ ዘሮች ተደራሽ ለማድረግ ተጨማሪ አቅም እንደሚሆን ጠቁመዋል።


በክልሉ የግብርናውን ዘርፍ የመልማት አቅም በምርምር በማስደገፍ ውጤታማ ለማድረግ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሠራ መሆኑን ያነሱት ደግሞ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ማስረሻ በላቸው ናቸው።

ለዚህም የምርምር ማዕከላትን በሰው ኃይልና በግብዓት በማደራጀት ውጤታማ እንዲሆኑ ከማድረግ ጎን ለጎን ተደራሽነታቸው ላይ መሠራቱን ጠቅሰዋል።


ይህም ለአርሶ አደሮች በምርምር የወጡ የግብርና ማሳደጊያዎችን በማቅረብ ምርታማነትን በማሳደግ፣ ከምግብ ፍጆታ አልፎ የውጭ ምንዛሬ የሚያስገኙ ምርቶች ላይ እንዲሳተፉ እንደሚያግዝም አስረድተዋል።

ምርታማነታቸው በማደጉም ራሳቸውን መጥቀምና አገርም ከዘርፉ ማግኘት የሚገባትን ጥቅም እንድታገኝ መሥራት ይገባል ብለዋል።

የክልሉ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ አማኑኤል ኃይሌ በበኩላቸው፣ የማዕከሉ መገንባት ኢንስቲትዩቱ ለሚያከናውናቸው ተግባራት ተጨማሪ አቅም የሚፈጥር መሆኑን ገልጸዋል።


ተቋሙ በሰብል፣ በእንስሳትና በተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ላይ ያተኮሩ ችግር ፈቺ የምርምር ሥራዎችን በቀጥታ ወደ አርሶና አርብቶ አደሩ ተደራሽ በማድረግ ሚናውን የሚወጣ መሆኑን ነው የተናገሩት።

ለሕንጻ ግንባታው አጠቃላይ ከ137 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ እንደተደረገበት ገልጸው፤ ማዕከሉ የጀመራቸውን ሥራዎች አስፍቶና አጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።

የዳውሮ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዳዊት ገበየሁ፣ የማዕከሉ መገንባት የግብርና ምርታማነትን በማሳደግ ረገድ ለአካባቢው አርሶ አደር ትልቅ ጠቀሜታ እንዳለው ጠቅሰው፣ የተጀመሩ ሥራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ጠይቀዋል።


በምረቃው ሥነ-ሥርዓት የክልሉ የመንግሥት ዋና ተጠሪ አቶ ፍቅሬ አማንን ጨምሮ ሌሎች የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች እንዲሁም የአካባቢው ነዋሪዎች ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው

ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...

May 15, 2026

በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ ነው -ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚው ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለአፍሪካ አገራት ትልቅ አርአያ ናቸው - የላይቤሪያ ልዑካን ቡድን

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...

Apr 16, 2026

ሀገራዊ ለውጡ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ማህበራዊ ትስስር ጠንካራ መሰረት የጣለ ነው - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...

Apr 3, 2026