🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፦የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ከዓለም የከተሞች ፎረም ተሳትፎ ጎን ለጎን የአዘርባጃን የአሳን ቀላል የአንድ ማዕከል ዲጂታል አገልግሎትን ጎብኝተዋል።
ከንቲባ አዳነች አቤቤ የኢትዮጵያ ልዑክ ከዓለም የከተሞች ፎረም ተሳትፎ ጎን ለጎን የአዘርባጃንን የ“አሳን” (ASAN-Azerbaijan Service and Assessment Network) ቀላል የአንድ ማዕከል ዲጂታል አገልግሎት መጎብኘቱን ጠቁመዋል።
ከንቲባዋ ባስተላለፉት መልዕክት፥ በኢትዮጵያ እስከአሁን በመሶብ ዲጂታል የአንድ ማዕከል አገልግሎት ከፍተኛ ለውጥ የመጣ ቢሆንም፣ አሁንም ልምድ ሊሆኑ በሚችሉ ጉዳዮች ላይ ውይይት መደረጉን ገልጸዋል።

ከ14 ዓመታት በፊት የተጀመረውና በቀን 40 ሺህ አፕሊኬሽን ላይ አገልግሎት የሚያሳልጠው “አሳን”፣ በአውቶቡሶች የሚሰጥ የገጠር አካባቢዎች ተንቀሳቃሽ የአገልግሎት ማዕከል በተደራጀ፣ ፈጣንና ቀላል መንገድ አገልግሎት የሚሰጥ መሆኑን ጠቁመዋል።
በኢትዮጵያም ከ41 በላይ ማዕከላት ተገንብተው ስራ የጀመሩ ሲሆን፣ ከነዚህም ውስጥ በአዲስ አበባ 6 ማዕከላት እና 1 ተንቀሳቃሽ አውቶቡስ የዲጂታል የአንድ ማዕከል አገልግሎት በመስጠት ላይ እንደሚገኙም ነው ከንቲባዋ ያወሱት።
በጉብኝቱ ወቅትም የ“አሳን” ሰራተኞች አገልግሎት ሲሰጡ ፈገግታ እና ትህትና አንዱ የአገልግሎት መለኪያ መሆኑን፣ የመከታተያ ካሜራዎች የተገጠሙ መሆኑን እና በጥሩ ሁኔታ የሚያገለግል ሰራተኛ ተመዝኖ የተገልጋዩ የዕርካታ መጠን ከፍተኛ ከሆነ ከደሞዝ በተጨማሪ ቦነስ እንደሚከፈለው ለመታዘብ መቻላቸውን ተናግረዋል።

በዛው ልክ ደግሞ በመስፈርቱ መሰረት ያላገለገለ ሰራተኛ ወዲያው እንደሚባረርና ለነገ ተስፋ አድገው ህዝባቸውን በከፍተኛ ትጋትና አክብሮት የሚያገለግሉ በርካታ በጎ ፍቃደኛ ወጣቶችንም መመልከታቸውን ገልጸዋል።
የእኛም ቢሮክራሲ በተጀመረው አግባብ ሙሉ በሙሉ እንደሚለወጥ እናምናለን ያሉ ሲሆን ይህ እንዲሳካም በትጋት እንደሚሰራ ከንቲባዋ አረጋግጠዋል።
ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...
May 15, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...
Apr 16, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...
Apr 3, 2026