የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

የሚቲዎሮሎጂ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችሉ ቴክኖሎጂዎችን ሥራ ላይ በማዋል ተጨባጭ ውጤቶች እየተገኙ ነው

May 15, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 7/2018 (ኢዜአ)፦ዓለም አቀፍ ስታንዳርድ የጠበቀ የሚቲዎሮሎጂ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችሉ ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችን ሥራ ላይ በማዋል ተጨባጭ ውጤቶች እየተገኙ መሆኑን የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት አስታወቀ።

የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር እና የዓለም ሚቲዎሮሎጂ ድርጅት የአፍሪካ አህጉር ፕሬዚዳንት አቶ ፈጠነ ተሾመ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ የኢንስቲትዩቱ የትንበያ አቅም በሰው ኃይል፣ በቴክኖሎጂ መሠረተ ልማት ዝርጋታና በተደራሽነት ረገድ ወደ ላቀ ደረጃ እየተሸጋገረ ይገኛል።

በአሁኑ ወቅትም የአጭር፣ የመካከለኛና የረጅም ጊዜ የአየር ሁኔታ ትንበያዎችን ለውሳኔ ሰጪ አካላትና ለተጠቃሚው ማኅበረሰብ በወቅቱ ተደራሽ እያደረገ መሆኑንም ገልጸዋል።

ኢንስቲትዩቱ ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ የሚቲዎሮሎጂ አገልግሎት ለመስጠት ካስቀመጠው ግብ አንጻር፣ ግቡን ለማሳካት የሚያስችሉ ሁለንተናዊ የሚቲዎሮሎጂ ምልከታ መሠረተ ልማቶች በአገር አቀፍ ደረጃ መዘርጋታቸውን ጠቁመዋል።


የአየር ሁኔታን በቅርበት ለመከታተል የሚያስችሉ ዘመናዊ ራዳሮች በአራት ስትራቴጂካዊ የአገሪቱ አካባቢዎች ላይ ተተክለው በቅርቡ ወደ ሥራ መግባታቸውን ጠቁመዋል፡፡

ራዳሮቹ የተተከሉባቸው ቀጠናዎች በሰሜን ምዕራብ ኢትዮጵያ፣ በምዕራብ ኢትዮጵያ፣ በመካከለኛው ኢትዮጵያ እና በደቡብ ኢትዮጵያ መሆናቸውን ጠቅሰዋል፡፡

እነዚህ ዘመናዊ ራዳሮች በተተከሉበት ስፍራ ዙሪያ እስከ 250 ኪሎ ሜትር ክብ ርቀት (ራዲየስ) ውስጥ ያለውን ማንኛውንም የሚቲዎሮሎጂ ለውጥና መረጃ በቀጥታ ወደ ማዕከላዊ የመረጃ ቋት የመላክ ከፍተኛ አቅም እንዳላቸው አብራርተዋል።

ከራዳር ዝርጋታው በተጨማሪ፣ የአየር ንብረት መረጃዎችን በከፍተኛ ፍጥነት ወደ መረጃ ቋት የመላክ አቅም ያላቸው የ‘አውቶማቲክ ዌዘር ስቴሽኖች’ ተከላ እየተካሄደ መሆኑን አንስተዋል።


እነዚህ ወደ ሥራ የገቡና እየተዘረጉ ያሉ ቴክኖሎጂዎች ዓለም የደረሰበትን ከፍተኛ የሚቲዎሮሎጂ ምልከታ ደረጃ የጠበቁ መሆናቸውን ጠቅሰው፤ በዚህም የአገሪቱን የትንበያና የቅድመ ማስጠንቀቂያ አቅም በማጎልበት ረገድ የሚጫወቱት ሚና ከፍተኛ መሆኑን ገልጸዋል።

ቴክኖሎጂዎቹ ተደራሽነትን ከማስፋታቸውም በላይ ማኅበረሰቡ ወቅቱን የጠበቀና አስተማማኝ አገልግሎት እንዲያገኝ እንደሚያስችሉ አስገንዝበዋል።

የቴክኖሎጂ ውጤቶቹ ለግብርናው ክፍለ ኢኮኖሚ፣ በአየር ንብረት ለውጥ ሳቢያ ሊከሰት የሚችለውን ጉዳት በቅድመ ማስጠንቀቂያ ለመቀነስ ብሎም ለሌሎች መሠረታዊ ጉዳየች ያላቸው ፋይዳ የጎላ ነው፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው

ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...

May 15, 2026

በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ ነው -ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚው ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለአፍሪካ አገራት ትልቅ አርአያ ናቸው - የላይቤሪያ ልዑካን ቡድን

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...

Apr 16, 2026

ሀገራዊ ለውጡ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ማህበራዊ ትስስር ጠንካራ መሰረት የጣለ ነው - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...

Apr 3, 2026