የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

በከተማዋ ለባለይዞታዎች በቴክኖሎጂ የተደገፈ የዲጂታል ካርታ እየተዘጋጀ ነው

May 7, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ጎንደር ፤ሚያዝያ 29/2018 (ኢዜአ)፦በጎንደር ከተማ ከ45 ሺህ በላይ የቤትና የቦታ ባለይዞታዎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ በቴክኖሎጂ የተደገፈ የዲጂታል ካርታ ዝግጅት እየተከናወነ መሆኑን የከተማዋ መሬት መምሪያ አስታወቀ።

የዲጂታል ካርታው አሰራር በመሬት አስተዳደር ዙሪያ የሚታዩ የአገልግሎት አሰጣጥ ችግሮችን ለመፍታትና ዘመናዊ አሰራርን ለማስፈን ያለመ እንደሆነም ተገልጿል።

የከተማው መሬት መምሪያ ምክትል ሃላፊ አቶ አዛናው መልካሙ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ የዲጂታል ካርታው በዘርፉ የሚስተዋለውን የነዋሪዎች የመልካም አስተዳደር ቅሬታ ከመሠረቱ በሚፈታ መልኩ እየተከናወነ ነው።

በስድስት ክፍለ ከተሞች የሚገኙ የቤትና የቦታ ይዞታዎችን ወደ ዲጂታል የካርታ አሰራር ስርአት ለመቀየር መረጃን በመሰብሰብ፣ በማደራጀትና በማጣራት ወደ መረጃ ቋት የማስገባት ስራ መጀመሩን ገልጸዋል፡፡

ባለፉት ዘጠኝ ወራትም ከአራት ሺህ በላይ የከተማ ቦታና ቤት ባለይዞታዎችን በመመዝገብ ከ300 በላይ ለሚሆኑ ባለይዞታዎች ዲጂታል ካርታ ማስረከብ መቻሉን ተናግረዋል፡፡

ዲጂታል ካርታው ህጋዊነቱ የተረጋገጠ ይዞታ እንዲኖራቸው ከማድረግ ባለፈ ቀደም ሲል ይፈጸሙ የነበሩ በካርታ ላይ ካርታ የመስጠት፣ መረጃ የማጥፋትና የስርቆት ድርጊቶችን ለማስቀረት የሚያስችል ነው ብለዋል።

ህገ ወጥ የመሬት ወረራን ለመከላከልና ውድ ሃብት የሆነውን መሬት በአግባቡ ይዞ ለሚፈለገው ልማት ለማዋል ጭምር ፋይዳው የጎላ መሆኑንም አስረድተዋል።

የዲጂታል ካርታ ስርአቱን ከከተማው የስማርት ሲቲ ተግባራት ጋር በማቀናጀት በቅርቡ ከተጀመረው የዲጂታል የመኖሪያ ቤት መለያ ቁጥር አሰጣጥ ጋር በማስተሳሰር የሚፈጸም መሆኑን አብራርተዋል፡፡

መምሪያው በጥናት የተለዩትን የባለይዞታዎች መረጃን ወደ ዲጂታል የመረጃ ስርአት በመቀየር ዲጂታል ካርታን ተደራሽ የማድረግ ስራውን በሚቀጥለው ዓመት ለማጠናቀቅ እየሰራ መሆኑን አስገንዝበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው

ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...

May 15, 2026

በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ ነው -ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚው ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለአፍሪካ አገራት ትልቅ አርአያ ናቸው - የላይቤሪያ ልዑካን ቡድን

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...

Apr 16, 2026

ሀገራዊ ለውጡ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ማህበራዊ ትስስር ጠንካራ መሰረት የጣለ ነው - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...

Apr 3, 2026