🔇Unmute
አዲስ አበባ፣ሚያዚያ 26/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በሰው ሰራሽ አስተውሎት (ኤ አይ) ዘርፍ ያላትን ተጠቃሚነት ይበልጥ ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ወርቁ ጋቸና (ዶ/ር)፡፡
ፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ከኢትዮጵያ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩትና ከእሑድ ኤ አይ ስቱዲዮ ጋር በመተባበር ያዘጋጀው የኤ አይ ሙዚቃ ውድድር ተካሂዷል፡፡
ወርቁ ጋቸና (ዶ/ር) በዚህ ወቅት እንደሉት ኢትዮጵያ በሰው ሰራሽ አስተውሎት (ኤ አይ) ዘርፍ ያላትን ተጠቃሚነት ይበልጥ ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ ነው፡፡
የሰው ሰራሽ አስተውሎት አሁን ላይ በተለያዩ የዓለም ሀገራት ችግሮች የሚፈቱበት ቁልፍ መሳሪያ እየሆነ መምጣቱን አስረድተዋል፡፡

ኤ አይ የሰው ልጅን የማሰብ፣ የመገንዘብ፣ የማመዛዘን፣ የማቀድ፣ የመማርና ቋንቋን የመረዳት አቅምን በማሳደግ የተለያዩ ተግባራትን በጥራትና በፍጥነት ለማከናወን ያስችላል ብለዋል፡፡
ቴክኖሎጂው በጥበብና መዝናኛው ዘርፍ ያለውን አስተዋጽኦ ይበልጥ ለማጠናከር በቅንጅት መስራት እንደሚገባ ነው አጽንኦት የሰጡት፡፡
የሰው ሰራሽ አስተውሎት አዲስ መሳሪያ ብቻ ሳይሆን ለችግሮች አዲስ የመፍትሄ ሃሳብ ማመላከቻ መንገድ በመሆን በዘርፉ ይዘቶችን በፍጥነት ለማዘጋጀት አማራጭ ሃሳብ ይዞ መምጣቱን ጠቅሰዋል፡፡
ተቋማቸው ኤ አይ ቴክኖሎጂን በሚገባ የተረዳ እና ለበጎ አላማ የሚጠቀም የሰው ሃይል ለማፍራት እየሰራ እንደሚገኝ አብራርተዋል፡፡

የኤ አይ ሙዚቃ ውድድሩ የዚሁ ሥራ አካል መሆኑን ጠቁመው ይህም ቴክኖሎጂው በጥበብ ዘርፍ ያለውን አቅም ከማሳየት ባለፈ በኢትዮጵያ ታሪክ የቴክኖሎጂና ጥበብን ጥምረት መግለጽ ያስቻለ ነው ብለዋል፡፡
ለአንድ ወር ሲካሄድ የቆየው የኤ አይ ሙዚቃ ውድድር በጎ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ፈጠራ ትግበራን በማበረታታት ወጣቶች ቴክኖሎጂውን በሃላፊነትና በሥነ ምግባር እንዲጠቀሙ ለማስቻል ያለመ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ውድድሩ በሙዚቃ ባለሙያዎች እና በዘርፉ ሥራ ፈጣሪዎች መካከል ያለውን ትብብር ይበልጥ እንደሚያጠናክር አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡
በመርሐ ግብሩ በሰው ሰራሽ አስተውሎት የይዘት ፈጠራ ክህሎት ያላቸው ወጣቶች መኖራቸውን መረዳት እንደተቻለ ጠቁመው በሒደቱ የተገኘው ውጤት አበረታች እንደሆነም አስገንዝበዋል፡፡
ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...
May 15, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...
Apr 16, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...
Apr 3, 2026