የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

በኢትዮጵያ በሰው ሰራሽ አስተውሎት ዘርፍ የተመዘገቡ ስኬቶች ለአህጉራዊ መሪነት መሰረት ሆነዋል

May 6, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 23/2018 (ኢዜአ)፦በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት በሰው ሰራሽ አስተውሎት የተመዘገቡ ስኬቶች ለኢትዮጵያ የዘርፉ አህጉራዊ መሪነት መሰረት መሆናቸውን የፌዴራል ሕግና ፍትህ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አምባሳደር ደግፌ ቡላ ገለጹ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአፍሪካ ኅብረት የሰው ሰራሽ አስተውሎት እና የዲጂታል ጤና ዘርፍ መሪ (Champion) ሆነው ተሹመዋል።

ሹመቱ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዘርፉ ላሳዩት አመራርና ኢትዮጵያ በአህጉሪቱ የሰው ሰራሽ አስተውሎትንና የፈጠራ ሥራዎችን ለማስፋፋት እየተገበረች ላለው የላቀ ሚና የተሰጠ እውቅና መሆኑ ተገልጿል።

ኢትዮጵያ ሰው ሰራሽ አስተውሎትን ሥነ-ምግባራዊ መርሆች በተከተለ መልኩ በማልማት፣ በመመራመር እንዲሁም ተግባራዊ በማድረግ በኩል ከአፍሪካ ቀዳሚዋ ሀገር እንድትሆን ለተሠሩ ሥራዎች እውቅና የሰጠ ነው ተብሏል።

የፌዴራል ሕግና ፍትህ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አምባሳደር ደግፌ ቡላ ለኢዜአ እንደተናገሩት፤ ኢትዮጵያ የአሠራር ሥርዓቷን ዲጂታል ለማድረግ እያከናወነች ያለችው ስራ በከፍተኛ የዕድገት ደረጃ ላይ ይገኛል፡፡

እንዲሁም ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራትም እንደ ትልቅ ተሞክሮ ሊወሰድ የሚችል መሆኑን ገልፀዋል።

ለዚህም ማሳያ እንዲሆን በስኬት የተጠናቀቀውን 'ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025' ስትራቴጂ እና በአሁኑ ወቅት ተግባራዊ እየተደረገ የሚገኘውን 'ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030' ስትራቴጂን በአብነት ጠቅሰዋል።

በተለይም በመንግሥት ተቋማት ውስጥ የአሰራር ቅልጥፍናን ለማምጣት እየተተገበረ ያለው የዲጂታል መንግሥታዊ አሠራር (e-government) ሥርዓት፣ ተጨባጭ ውጤት እያመጣ መሆኑን አስረድተዋል።

ይህም ለዜጎች የሚሰጡ አገልግሎቶችን ለማዘመንና ተደራሽ ለማድረግ ጉልህ ሚና እየተጫወተ እንደሚገኝ አስገንዝበዋል።

ኢትዮጵያ በሰው ሰራሽ አስተውሎት ዘርፍ እያከናወነች ያሉ ውጤታማ ሥራዎች እውቅና እያገኙ መምጣታቸውን ጠቅሰዋል፡፡

ለዚህም በቅርቡ የአፍሪካ ህብረት ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ዘርፉን በአህጉር ደረጃ እንዲመሩ የሰጠው ሹመት የኢትዮጵያን ስኬትና አርዓያነት የሚያሳይ ነው ብለዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዘርፉ ያላቸውን ጥልቅ እውቀትና የዳበረ ልምድ መሠረት በማድረግ፣ ኢትዮጵያ በዲጂታል ዘርፍ ውጤታማ እንድትሆንና የለውጥ እርምጃዎችን እንድታፋጥን ቁልፍ የአመራርነት ሚና እየተጫወቱ እንደሚገኙ አስረድተዋል።

የዲጂታል ሥርዓት ግንባታ የሀገሪቱን ተጠቃሚነት ከማረጋገጥ ባለፈ፣ ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራትም አርዓያ የሚሆንና አህጉራዊ የጋራ ብልጽግናን ለማምጣት ተስፋ የሚሰጥ መሆኑን አብራርተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው

ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...

May 15, 2026

በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ ነው -ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚው ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለአፍሪካ አገራት ትልቅ አርአያ ናቸው - የላይቤሪያ ልዑካን ቡድን

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...

Apr 16, 2026

ሀገራዊ ለውጡ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ማህበራዊ ትስስር ጠንካራ መሰረት የጣለ ነው - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...

Apr 3, 2026