የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ፖለቲካ እና ደህንነት

ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ባካሄደው የሪፎርም ትግበራ በቴክኖሎጂ የታገዘ ቀልጣፋ የፍትሕ አገልግሎት እየሰጠ ነው

Apr 24, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ባሕርዳር፤ ሚያዝያ 15/2018 (ኢዜአ)፡- ተቋማቸው ባካሄደው የሪፎርም ትግበራ በቴክኖሎጂ የታገዘ ቀልጣፋ የፍትሕ አገልግሎት መስጠት መቻሉን የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ዓለምአንተ አግደው ገለጹ።

የጠቅላይ ፍርድ ቤቱ የዘጠኝ ወራት የዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ ተካሂዷል።


በዚሁ ወቅትም አቶ ዓለምአንተ እንደገለጹት፤ የፍርድ ቤቶችን አገልግሎት ዲጂታላይዝ ለማድረግ የተቀረጸው የሦስት ዓመት ስትራቴጂ አተገባበር ተስፋ ሰጭ ውጤቶችን እያሳየ መሆኑን ተናግረዋል።

በመጀመሪያው ምዕራፍ የታቀዱ የመሠረተ-ልማት ዝርጋታ፣ የኔትወርክ ሥራዎች እና የስማርት ችሎቶች ግንባታ ሥራዎች በስኬት መከናወናቸውን አንስተዋል።

ይህም ባለጉዳዮች ባሉበት ሆነው በኢ-ፋይሊንግ ሥርዓት ክስ መመስረት፣ ይግባኝ መጠየቅና የጉዳያቸውን ሂደት በሞባይል መተግበሪያ መከታተል የሚያስችል ዘመናዊ አሠራር ሥራ ላይ መዋሉን አስረድተዋል።


በቪዲዮ ኮንፈረንስ የሚታገዙ ስማርት ችሎቶች በመዘርጋታቸውም ሕብረተሰቡ ካለበት ሆኖ ክርክሩን እንዲያካሂድ በማድረግ የባለጉዳዮችን ወጪና እንግልት መቀነስ ተችሏል ነው ያሉት።


የጠቅላይ ፍርድ ቤቱ የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ ዳይሬክተር መኳንንት አገኘሁ (ዶ/ር)፤ የፍርድ ቤቶችን አሠራር ዘመናዊ በማድረግ ቀልጣፋና ፍትሐዊ አገልግሎት ለመስጠት፣ የፍትሕ ተደራሽነትን ለማስፋት፣ የዳኝነት አገልግሎት ጥራትን በማሻሻል የሕዝብን እርካታ ለማረጋገጥ ያስቻሉ ተግባራት ተከናውነዋል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው

ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...

May 15, 2026

በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ ነው -ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚው ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለአፍሪካ አገራት ትልቅ አርአያ ናቸው - የላይቤሪያ ልዑካን ቡድን

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...

Apr 16, 2026

ሀገራዊ ለውጡ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ማህበራዊ ትስስር ጠንካራ መሰረት የጣለ ነው - ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...

Apr 3, 2026