🔇Unmute
መጋቢት 24 በኢትዮጵያ የፖለቲካ ውስጥ አዲስ ምዕራፍን የከፈተ የለውጥ ምዕራፍ ጅማሮ ማብሰሪያ ነው።
ለውጡም በፈተናዎች ውስጥ ኢትዮጵያን ወደ ከፍታ የሚያሻግሩ በርካታ ስኬቶችን በማስመዝገብ ዘልቋል፡፡
ላለፉት 8 የለውጥ አመታት ትኩረት ከተሰጣቸው ዘርፎች መካከል አንዱ የመንገድ መሰረተ ልማት ነው።
በሀረሪ ክልልም ለመንገድ መሰረተ ልማት በተሰጠው ትኩረትና በተከናወኑ ተግባራት የህዝቡን የመንገድ መሰረተ ልማት ችግር የቀረፉ በርካታ ስኬቶች መመዝገባቸውን የክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ አስታውቋል።

በተለይም ገጠሩን ከከተማው ጋር በማስተሳሰር በከተማ እና ገጠር ፍትሀዊ የሆነ የመሰረተ ልማት ተደራሽነት እንዲኖር ለማስቻል ዘርፈ ብዙ ስራዎች መከናወናቸውን ገልጿል።
በዚህም ወረዳን ከወረዳ ብሎም ገጠሩን ከከተማ ጋር የሚያገናኙ የአስፓልት እና የጠጠር መንገዶች ተገንብተው ለአገልግሎት ክፍት ተደርገዋል።
ይህም አርሶ አደሩ ምርቱን በቀላሉ ለገበያ ማቅረብ እንዲችል፤ እንግልትና የምርት ብክነት መቀነሱ ተመላክቷል።
በከተማም የተገነቡ የመንገድ መሰረተ ልማቶች የትራንስፖርት እንቅስቃሴው የተሳለጠ እንዲሆን ከማስቻል በተጨማሪ የተገነቡ ምቹ የእግረኛ መንገዶች የዜጎችን ደህንነት ከማረጋገጥ ባሻገር ከተማዋን የተሻለ ገፅታ አላብሰዋል።

የመንገድ ፕሮጀክቶቹ ገፅታ ከመቀየር ባሻገር የየአካባቢው ኢኮኖሚ እንዲነቃቃ ማድረጉ ተገልጿል።
የለውጡ መንግሥት ለህዝቡ ቃል በገባው መሰረት ፕሮጀክቶችን በአጭር ግዜ ጀምሮ በጥራት እና ፍጥነት ማጠናቀቅ መገለጫው ሆኗል።
እውን የሆኑ ፕሮጀክቶች ጊዜን ብቻ ማእከል ያደረጉ ሳይሆኑ ጥራትን ጨምረው ዘመን ተሻጋሪነትን ማዕከል ተደረገው የተገነቡ ናቸው።

በለውጡ አመታት በመንገድ መሰረተ ልማት የተሰሩ ስራዎችም ህዝቡ ለዘመናት ሲያነሳቸው የቆዩ ጥያቄዎች ምላሽ እንዲያገኝ ያስቻሉ መሆናቸውን ነው ቢሮው ያስታወቀው።
የክልሉ መንግስት ለመንገድ መሰረተ ልማት ልዩ ትኩረት በመስጠት እያከናወናቸው የሚገኙ ስራዎችን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጿል።
ሀዋሳ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች ከተረጅነት የመውጣት ጥረትን ለማሳካት የሚያስችል ተጨባጭ ውጤት እያመ...
May 15, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኦዲት ዘርፍ በተከናወኑ የሪፎርም ተግባራት ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆናቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሠረት ዳምጤ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 7/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ በምግብ ዋስትና እና በኢኮኖሚ ልማት ዘርፍ እያከናወነቻቸው ያሉ ተግባራት ለመላው አፍሪካ አገራት ትልቅ አ...
Apr 16, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 24/2018 (ኢዜአ)፦ ሀገራዊ ለውጡ የሀገሪቱን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራቶች በመጠገን፣ ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ ከፍታና ለማህበራዊ ትስስ...
Apr 3, 2026