የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

የአዲስ አበባ የልማት ስኬቶች ለአፍሪካውያን 'እኛም እንችላለን' የሚል ተነሳሽነትን የሚፈጥሩ ናቸው

Apr 22, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 13/2018(ኢዜአ)፦ የአዲስ አበባ የመሰረተ ልማት ስኬቶች ለአፍሪካውያን 'እኛም እንችላለን' የሚል ተነሳሽነትን የሚፈጥሩና የሚያኮሩ ናቸው ሲሉ ከተለያዩ አፍሪካ ሀገራት የተውጣጡ ባለሙያዎች ገለጹ።

በአዲስ አበባ ባለፉት ጥቂት ዓመታት የታዩት ግዙፍ ለውጦች ከተማዋን የአፍሪካ የዲፕሎማሲ እና የንግድ መዲናነት ወደ ላቀ ደረጃ ያሸጋገሩ ናቸው።

ለአብነትም የኮሪደር ልማት ስራዎች፣ ዘመናዊ የትራንስፖርት መሰረተ ልማት ዝርጋታ፣ የወንዝ ዳርቻ ልማት ስራዎችና የአገልግሎት ዘርፍ ሽግግርና ሌሎች የተገኙ ውጤቶች ይጠቀሳሉ።


15ኛው የምስራቅና ደቡብ አፍሪካ ሀገራት የጋራ ገበያ (ኮሜሳ) ሴክሪቴሪያት የቴክኒካል ኮሚቴ አህጉራዊ ስብሰባ በቅርቡ በአዲስ አበባ ተካሂዷል።

በጉባኤው የተሳተፉ ከተለያዩ አፍሪካ ሀገራት የተውጣጡ ባለሙያዎች ለኢዜአ እንደገለጹት፤ አዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረት መቀመጫ፥ የአፍሪካ ዲፕሎማሲ ማእከል መሆኗን በተግባር ማሳየት ተችሏል።

በተጨማሪም አዲስ አበባ ለተለያዩ ዓለም አቀፍ ድርጅቶች እና ለልማት አጀንዳዎች ምቹ ሁኔታን በመፍጠር በኩል ያሳየችው ብቃት የሚደነቅ መሆኑን ገልጸዋል።

ለከተማዋ ነዋሪዎችና ለዲፕሎማቲክ ማህበረሰቡ የሚመጥን የአረንጓዴ ልማት፣ ዘመናዊነትና ውበት እንዲሁም ዘመናዊ የአሰራር ስርዓት በመዘርጋት የተከናወኑ ስራዎች በቅርብ ዓመታት የተገኙ ለውጦች የሚደነቁ መሆናቸውንም ተናግረዋል።

ይህም ለአፍሪካውያን "እኛም እንችላለን" የሚል ተነሳሽነትን የሚፈጥርና የሚያኮራ ስራ ነው ብለዋል።


ከዛምቢያ የመጡት ማርያ ዲየን ፔሪ (ዶ/ር) በአዲስ አበባ ከተማ ከአመታት በፊት ይኖሩ እንደነበረ ገልጸው፤ በአሁኑ ወቅት በከተማዋ ባዩት ሁሉን አቀፍ ለውጦች መደነቃቸውን ተናግረዋል።

አዲስ አበባ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ አጀንዳዎች ላይ የሚካሄዱ ጉባኤዎችን በማስተናገድ ጉልህ ሚና እያበረከተች እንደምትገኝ ይገልጻሉ።

በመሰረተ ልማት ግንባታና በሎጂስቲክስ አገልግሎትም አስደናቂ ለውጦች መገኘታቸውንም ጠቁመዋል።

ሌላው ከዛምቢያ የጉባኤው ተሳታፊ ቺጋጉራ ሚቲ በአሁኗ አዲስ አበባ እና ቀደም ሲል በነበረችው ከተማ መካከል ያለው ልዩነት እጅግ ሰፊ ነው ብለዋል።


አዲስ አበባ አህጉራዊ አቅምን የአፍሪካ ባለሙያዎች ትልቅ ችሎታ የምታሳይ ምሳሌ መሆኗንም አክለዋል።

ዘመናዊ የአሰራር ስርዓትን በማስፋፋት የንግድ እና የዲፕሎማሲ ስራዎችን በፈጣን ሁኔታ ማከናወን የሚያስችሉ ስርዓቶች መዘርጋታቸውንም አንስተዋል።

ኢትዮጵያ ሰዎች ራእይና ቁርጠኝነት ካላቸው ተአምር መስራት እንደሚቻል የምታሳይ ምሳሌ ናት ሲሉም ተናግረዋል።

ከቡሩንዲ የመጣችው ሊስ ኤስታ ካራኩቲማ በበኩሏ አዲስ አበባ በዲፕሎማሲ፣ በቴክኖሎጂ፣ በመሰረተ ልማትና በሌሎች ዘርፎች ለአፍሪካ ሀገራት አርአያ ናት ብላለች።


በኢትዮጵያ ፕሮጀክቶችን በአጭር ጊዜ የማጠናቀቅ ልምድ ማዳበርንና ዘመናዊ የአሰራር ስርዓትን በመዘርጋት የተሰሩ ስራዎች በአጭር ጊዜ የተገኙ ውጤቶች ተነሳሽነትን እንደሚፈጥሩም ገልጻለች።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ባለፉት 10 ወራት ከወጪ ንግድ 8 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ተገኝቷል

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ባለፉት 10 ወራት ከወጪ ንግድ 8 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ማግኘት መቻሉን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁ...

May 15, 2026

ረቂቅ አዋጁ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ ይኖረዋል

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...

Apr 23, 2026

ኢትዮጵያ እና አይኤምኤፍ በኢኮኖሚው መስክ ትብብራቸውን ያጠናክራሉ

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...

Apr 17, 2026

በጀጎል ግንብ ውስጥ የሚገነባው የ”ዳር ሀረር” የመልሶ ማልማት ፕሮጀክት ግንባታ ሊጀመር ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...

Apr 12, 2026