🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ህዳር 3/2018(ኢዜአ)፡- በ2018 በጀት ዓመት እስካሁን በተሰራ ስራ 2ሺህ 96 ነጥብ 37 ቶን እሸት ቡና መሰብሰቡን የወላይታ ዞን ግብርና መምሪያ አስታወቀ።
በበጀት ዓመቱ 7ሺህ 880 ቶን እሸት ቡና ለመሰብሰብ ታቅዶ ወደ ሥራ መገባቱን የመምሪያው ምክትል እና የቡናና ቅመማቅመም ዘርፍ ኃላፊ ከአብነህ ተስፋዬ ለኢዜአ ገልጸዋል።

በዚህም እስካሁን 2ሺህ 96 ነጥብ 37 ቶን እሸት ቡና መሰብሰቡን ገልጸው፤ አሁንም ወደ ማዕከላዊ ገበያ የሚላክ ቡና በተለያዩ ግብይቶች እየተሰበሰበ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
በሌላ በኩል 8 ነጥብ 9 ቶን የታጠበ እንዲሁም 343 ነጥብ 5 ቶን ያልታጠበ የተቀሸረ ቡና ወደ ማዕከላዊ ገበያ መላኩን ገልጸዋል።
በአሁኑ ወቅትም ብክነት እንዳይኖር የደረሰ ቡና ከስር ከስር በቅንጅት እየተሰበሰበ መሆኑንም አመላክተዋል።
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ባለፉት 10 ወራት ከወጪ ንግድ 8 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ማግኘት መቻሉን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁ...
May 15, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...
Apr 23, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...
Apr 17, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...
Apr 12, 2026