🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 17/2018 (ኢዜአ)፡- በ2018 የበጀት ዓመት 21 ከተሞች ወደ ስማርት ሲቲ ትግበራ እንዲገቡ የሚያስችሉ አሠራሮች መጠናከራቸውን ከተማና መሠረተ-ልማት ሚኒስቴር አስታወቀ።
በሚኒስቴሩ የአከታተም ጥናትና የሕግ ማዕቀፍ ዝግጅት ዴስክ ኃላፊ አስማማው ምኑዬ ለኢዜአ እንዳሉት፤ አዳማ፣ ባሕርዳርና ሐዋሳ ከተሞች ቀደም ብለው ወደ ስማርት ሲቲ ትግበራ ገብተዋል።
በያዝነው የበጀት ዓመትም 21 ከተሞች ወደ ስማርት ሲቲ ትግበራ እንዲገቡ ድጋፍ እየተደረገ ነው ብለዋል።
የስማርት ሲቲ ግንባታና መመዘኛ ሠነድ ተዘጋጅቶ ለክልሎችና ከተማ አሥተዳደሮች መሰራጨቱን ጠቅሰዋል።
ስማርት ኢኮኖሚ፣ ስማርት አሥተዳደር፣ ስማርት አካባቢ፣ ስማርት ሞቢሊቲ፣ ስማርት ነዋሪና ስማርት አኗኗር የተሰኙ ስድስት የስማርት ሲቲ ምሰሦዎች በስማርት ሲቲ ስትራቴጂው ላይ መቀመጣቸውንም አስረድተዋል።
በእያንዳንዱ ምሰሦ ላይም ነዋሪዎችን ተጠቃሚ የሚያደርጉ አሠራሮች መኖራቸውን ነው ያስረዱት።
ስማርት ሲቲ ነዋሪዎች ባሉበት ሆነው በ ‘ኦንላይን’ እንዲሁም እንደ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ባሉ አሠራሮች በርካታ ተቋማትን በአንድ ስፍራ ማግኘት የሚያስችል መሆኑን አስገንዝበዋል።
ከተሞች ጽዱ፣ የእግረኛና ብስክሌት መንገዶች፣ የማረፊያ፣ የስፖርት ማዘውተሪያ እንዲኖራቸው እንደሚያስችልም ገልጸዋል።
ስማርቲ ሲቲ ተጀምሮ የሚያልቅ ሳይሆን ቴክኖሎጂው ባደገ ቁጥር የሚያድግ ሂደት መሆኑን ገልጸው፤ የአንድ ተቋም ሥራ ስላልሆነ ተቋማት፣ ባለድርሻ አካላትና ሕብረተሰቡ ትብብሩን እንዲያጠናክር ጠይቀዋል።
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ባለፉት 10 ወራት ከወጪ ንግድ 8 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ማግኘት መቻሉን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁ...
May 15, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...
Apr 23, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...
Apr 17, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...
Apr 12, 2026