🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 13/2018(ኢዜአ)፦የ”DESSU” ኮሪደር አስተዳደር ባለስልጣን የቴክኒክ ኮሚቴ እና የሚኒስትሮች ምክር ቤት መድረክ የ”DESSU” ኮሪደር አስተዳደር ባለስልጣንን ለማቋቋም በመስማማት ተጠናቋል።
የቴክኒክ ኮሚቴው እና የሚኒስትሮች ምክር ቤቱ መድረክ ጅቡቲን፣ ኢትዮጵያን፣ ደቡብ ሱዳንን እና ዩጋንዳን ያቀፈ ነው።

የ”DESSU” ኮሪደር አስተዳደር ባለስልጣንን ለመመስረት በጅቡቲ ከኦክቶበር 21-22/25 ለሁለት ቀናት ውይይት ሲያደርግ የቆየው የቴክኒክ ኮሚቴ እና የሚኒስትሮች ምክር ቤት የኮርደር አስተዳደር ባለስልጣን መቋቋም ላይ ተስማምቷል።
ከሁለት ሳምንት በኋላ በኢትዮጵያ በመገናኘት የአስተዳደሩን ሟቋቋሚያ ስምምነት ለመፈራረም በመግባባት እና የስምምነት ቃለ-ጉባኤ በመፈራረም ተጠናቋል።
የ”DESSU” ኮሪደር በአራቱ ሀገራት መካከል የውጪ ንግድ መንገዶችን በቀላሉ ለማገናኘት፣ መንገድ እና ሎጂስቲክስ አገልግሎትን ለማሳለጥ ያለመ ነው።
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ እና በሸገር ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦትን ማረጋገጥ የሚያስችል ዘመናዊ የመሰረተ ልማት ግንባ...
Mar 31, 2026
አዲስ አበባ ፤የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፦የኢትዮ-ጅቡቲ የባቡር ትራንስፖርት ተገልጋዮች ፋይዳ መታወቂያን ተጠቅመው በዲጂታል አማራጭ ትኬት የሚቆርጡበት አሰራር ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ ጥር 03/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለስልጣን የለማ የትራንስፖርት ኦፕሬተሮችንና የጭነት ባለቤቶችን የሚገናኝ መተግበሪያ አስጀምሯል። ...
Feb 12, 2025