የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ባለፉት ሶስት ወራት ውጤታማ የልማትና የመልካም አስተዳደር ተግባራት ተከናውነዋል - ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን

Oct 23, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አሶሳ፤ ጥቅምት 12/2018 (ኢዜአ)፦ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያዎቹ ሶሰት ወራት ውጤታማ የልማትና የመልካም አስተዳደር ተግባራት መከናወናቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን አስታወቁ።

የክልሉ የ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያው ሩብ ዓመት የዕቅድ አፈጻጸም የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት እየተገመገመ ነው።


በግምገማ መድረኩ ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን እንደተናገሩት፤ የመጀመሪያው ሩብ ዓመት የትምህርት ንቅናቄ በስፋት የተከናወነበት፣ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎትና የግብርና ስራ የተጠናከረበት ነው።

የሕብረተሰቡን የመልካም አስተዳደር ጥያቄ ለመፍታት መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በአጭር ጊዜ ወደ ስራ እንዲገባ መደረጉንና በዲጂታል የታገዘ አገልግሎት እየተሰጠ ነው ብለዋል።

በመጀመሪያ ሩብ ዓመት የማዕድን ዘርፉን ለማልማት እየተከናወነ ባለው ቅንጅታዊ ስራ 1ሺህ 709 ኪሎ ግራም ወርቅ ለብሔራዊ ባንክ ገቢ መደረጉን ጠቅሰዋል።

በመጀመሪያ ሩብ የበጀት ዓመት ለተከናወኑ ስራዎች ውጤታማነት ቅንጅታዊ አሰራር በመተግበሩ እንደሆነ ተናግረዋል።

የበጀት ዓመቱ የመጀመሪያው ሩብ ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት በክልሉ ፕላንና ልማት ቢሮ ኃላፊ ቃሲም ኢብራሂም እየቀረበ ሲሆን፤ በሪፖርቱ ላይ ጥልቅ ውይይት እንደሚደረግ ይጠበቃል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ባለፉት 10 ወራት ከወጪ ንግድ 8 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ተገኝቷል

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ባለፉት 10 ወራት ከወጪ ንግድ 8 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ማግኘት መቻሉን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁ...

May 15, 2026

ረቂቅ አዋጁ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ ይኖረዋል

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...

Apr 23, 2026

ኢትዮጵያ እና አይኤምኤፍ በኢኮኖሚው መስክ ትብብራቸውን ያጠናክራሉ

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...

Apr 17, 2026

በጀጎል ግንብ ውስጥ የሚገነባው የ”ዳር ሀረር” የመልሶ ማልማት ፕሮጀክት ግንባታ ሊጀመር ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...

Apr 12, 2026