🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያውያን ጀግንነታቸውን ሀገር በማልማትና በመቀየር ሊያሳዩ ይገባል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከፌዴራል እና ክልል አመራሮች ጋር የገጠር ኮሪደር ስራዎች ላይ ውይይት አድርገዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የዚህ ዘመን የኢትዮጵያውያን ጀግንነት ሀገርን በማልማትና በመቀየር እንዲሁም ህዝብን መቀየር ሊሆን እንደሚገባ ገልጸዋል።
ለም ሀገር እና መሬት ይዘን ልንለምን አይገባም፤ የልመና ታሪካችንና የዜጎችን ህይወት መለወጥ የምንችለው ተግቶ በመስራት ነው ብለዋል።
ኢትዮጵያውያን ለበጎ አላማ በመደመር በሀገር ደረጃ ተጨባጭ ለውጥ ለማምጣት መስራት እንዳለባቸውም ነው ያመላከቱት።
ቀጣዩ ትውልድ የተሻለ ነገር እንዲረከብ ዛሬ ላይ ጠንክሮ መስራት እንደሚያስፈልግም አስገንዝበዋል።

ለማህበረሰብ የሚታይ እና የሚጨበጥ ስራ ለመስራት የአመራር ቁርጠኝነት ወሳኝ እንደሆነ ጠቅላይ ሚኒስትሩ አመልክተዋል።
ውድድር በልማት እና በስራ ሊሆን ይገባል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ክልሎች ባለቸው አቅም በመስራት የዜጎችን ህይወት ከቀየሩ ያለ ምንም ጥርጥር የበለጸገች ኢትዮጵያን ማየት እንደሚቻል ተናግረዋል።
ኢትዮጵያውያውን አንችልም የሚለውን ሀሳብ እና አመለካከት መስበር ይገባናል፤ ኢትዮጵያውያን መቻላችንን ድሮም አሳይተናል አሁንም ችለን ማሳየት አለብን ብለዋል።
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ባለፉት 10 ወራት ከወጪ ንግድ 8 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ማግኘት መቻሉን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁ...
May 15, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...
Apr 23, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...
Apr 17, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...
Apr 12, 2026