የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

የኢትዮጵያ የባሕር በር መሻት ፍትሐዊ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነትን ከማስጠበቅ የሚመነጭ የብሔራዊ ጥቅም አጀንዳ ነው

Oct 11, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፡-የኢትዮጵያ የባሕር በር መሻት ፍትሐዊ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነትን ከማስጠበቅ የሚመነጭ የብሔራዊ ጥቅም አጀንዳ መሆኑን በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ ፈትሂ ማህዲ (ዶ/ር) ገለጹ።

ምክትል ሰብሳቢው ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ በተፈፀመባት ታሪካዊ ስህተትና ኢ-ፍትሐዊ ሁኔታ የባሕር በር አልባ ከሆኑ ሀገሮች መካከል አንዷ ለመሆን ተዳርጋለች።

ኢትዮጵያ ከቀይ ባሕር በቅርብ ርቀት የምትገኝና የብዙ ሕዝብ ባለቤት ሀገር መሆኗ የባህር በር ከሌላቸው ሀገራት የተለየ እንደሚያደርጋት ገልጸዋል።

በዓለም የንግድ ሥርዓት በሸቀጦች እንቅስቃሴ ግዙፍ ስፍራ በሚሰጠው የቀይ ባሕር ላይ የባህር በር ማጣት በሀገር የኢኮኖሚ ዕድገት ላይ ኪሳራው ብዙ መሆኑን አስረድተዋል።

የባሕር በር ባለመኖሩ ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ የገቢና ወጪ የንግድ ሥርዓት ለከፍተኛ ወጪ እንድትጋለጥ ማድረጉን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ የባሕር በር አልባነትም የኢኮኖሚ ዕድገትን ለማስቀጠል በሚደረገው ጥረት በገቢና ወጪ ንግድ ተወዳዳሪነትና በዜጎች ኑሮ ላይ ጫና እያሳደረ እንደሚገኝ አንስተዋል።

በዓለም አቀፍ የኢኮኖሚ ተወዳዳሪነት ሥርዓት ውስጥ ፍትሐዊ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የባሕር በርና የወደብ አገልግሎት ወሳኝ ሚና እንደሚጫወት አብራርተዋል።

ኢትዮጵያ የግዙፍ ኢኮኖሚና ከፍተኛ የሕዝብ ቁጥር ባለቤት እንዲሁም ለቀይ ባህር በቅርብ ርቀት የምትገኝ መሆኗ የባሕር በር ፍትሐዊ ጥያቄዋ የብሔራዊ ጥቅም አጀንዳና የህልውና ጉዳይ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል።

የባሕር በር መሻቷም ፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገትና ተጠቃሚነትን ከማሳለጥ የሚመነጭ፣ ቀጣናዊ የጋራ ተጠቃሚነትና ዓለም አቀፍ መርህን የተከተለ የብሔራዊ ጥቅም ጉዳይ መሆኑን አመልክተዋል።

የኢትዮጵያ የባሕር በር መሻት የምስራቅ አፍሪካ የኢኮኖሚ ትስስርን በማሳለጥ ቀጣናዊ ሰላምና ደኅንነትን ከማስጠበቅ ጋር የተቆራኘ ጭምር መሆኑንም አስገንዝበዋል።

የምስራቅ አፍሪካ ትስስርም የንግድ ልውውጥና የቱሪስት ፍሰትን በማጠናከር የቀጣናውን ዜጎች የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት በማሳደግ የጋራ ብልጽግናን ለማረጋገጥ ጉልህ ጠቀሜታ እንደሚኖረው ተናግረዋል።

የኢትዮጵያን በመርህ ላይ የተመሰረተ የባሕር በር ጥያቄም ለጋራ የኢኮኖሚ ዕድገት፣ ሰላምና ደህንነት የሚኖረውን ገንቢ ሚና በመገንዘብ የቀጣናው ሀገራት ተገቢውን ምላሽ ሊሰጡ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

የኢትዮጵያን የባሕር በር ፍላጎት እውን ለማድረግ የውስጥና የውጭ ዲፕሎማሲያዊ ጥረቶች ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው አብራርተዋል።

ዜጎችም የኢትዮጵያን የባሕር በር ጥያቄ አዎንታዊ ምላሽ ለማስገኘት በሚደረገው ጥረት ሁሉ የድርሻቸውን ገንቢ ሚና ሊወጡ እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ባለፉት 10 ወራት ከወጪ ንግድ 8 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ተገኝቷል

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ባለፉት 10 ወራት ከወጪ ንግድ 8 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ማግኘት መቻሉን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁ...

May 15, 2026

ረቂቅ አዋጁ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ ይኖረዋል

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...

Apr 23, 2026

ኢትዮጵያ እና አይኤምኤፍ በኢኮኖሚው መስክ ትብብራቸውን ያጠናክራሉ

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...

Apr 17, 2026

በጀጎል ግንብ ውስጥ የሚገነባው የ”ዳር ሀረር” የመልሶ ማልማት ፕሮጀክት ግንባታ ሊጀመር ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...

Apr 12, 2026