አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 19/ 2017 (ኢዜአ)፦ የአረብ ባንክ ለአፍሪካ ኢኮኖሚ ልማት (BADEA) ለአፍሪካ የልማት ስራዎች የሚያደርገውን ድጋፍና አጋርነት እንደሚቀጥል አስታወቀ።
የተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (ኢሴኤ) ዋና ፀሐፊ ክላቨር ጋቴቴ ከአረብ ባንክ ለአፍሪካ ኢኮኖሚ ልማት (BADEA) ፕሬዝዳንት አብደላ አልሙሳይቤህ ጋር ተወያይተዋል።
ዋና ፀሐፊው ኢሴኤ እና የአረብ ባንክ ለረጅም ጊዜ የቆየ ወዳጅነት እንዳለው ገልጸው ይህን አጋርነቱን የበለጠ ለማጠናከር እንደሚሰራም ተናግረዋል።
በውይይቱ ላይ ባንኩ በአፍሪካ ልማት የሚያደርገውን ኢንቨስትመንት የማጠናከር ፍላጎት እንዳለው መገለጹን ኢዜአ ከኮሚሽኑ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
የአረብ ባንክ ለአፍሪካ ኢኮኖሚ ልማት ፕሬዝዳንት አብደላ አልሙሳይቤህ በኢትዮጵያ የስራ ጉብኝት እያደረጉ መሆኑም ይታወቃል።
አዲስ አበባ ፤የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፦የኢትዮ-ጅቡቲ የባቡር ትራንስፖርት ተገልጋዮች ፋይዳ መታወቂያን ተጠቅመው በዲጂታል አማራጭ ትኬት የሚቆርጡበት አሰራር ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ ጥር 03/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለስልጣን የለማ የትራንስፖርት ኦፕሬተሮችንና የጭነት ባለቤቶችን የሚገናኝ መተግበሪያ አስጀምሯል። ...
Feb 12, 2025