የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

የአረብ ባንክ ለአፍሪካ ኢኮኖሚ ልማት ያለውን አጋርነት እንደሚያጠናክር ገለጸ

Jul 30, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 19/ 2017 (ኢዜአ)፦ የአረብ ባንክ ለአፍሪካ ኢኮኖሚ ልማት (BADEA) ለአፍሪካ የልማት ስራዎች የሚያደርገውን ድጋፍና አጋርነት እንደሚቀጥል አስታወቀ።

የተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (ኢሴኤ) ዋና ፀሐፊ ክላቨር ጋቴቴ ከአረብ ባንክ ለአፍሪካ ኢኮኖሚ ልማት (BADEA) ፕሬዝዳንት አብደላ አልሙሳይቤህ ጋር ተወያይተዋል።

ዋና ፀሐፊው ኢሴኤ እና የአረብ ባንክ ለረጅም ጊዜ የቆየ ወዳጅነት እንዳለው ገልጸው ይህን አጋርነቱን የበለጠ ለማጠናከር እንደሚሰራም ተናግረዋል።

በውይይቱ ላይ ባንኩ በአፍሪካ ልማት የሚያደርገውን ኢንቨስትመንት የማጠናከር ፍላጎት እንዳለው መገለጹን ኢዜአ ከኮሚሽኑ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።

የአረብ ባንክ ለአፍሪካ ኢኮኖሚ ልማት ፕሬዝዳንት አብደላ አልሙሳይቤህ በኢትዮጵያ የስራ ጉብኝት እያደረጉ መሆኑም ይታወቃል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.