የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

የኮሪደር ልማቱ ከተጎሳቆለ አካባቢ በማላቀቅ የተሻለ ህይወት እንድንመራ አስችሎናል- የመዲናዋ የመልሶ ማልማት ተነሺዎች

Jul 23, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ሐምሌ 15/2017(ኢዜአ)፦የኮሪደር ልማቱ ከተጎሳቆለ አካባቢ በማላቀቅ የተሻለ ህይወት ለመምራት እንዳስቻላቸው የመዲናዋ የመልሶ ማልማት ተነሺዎች ገለጹ።

አዲስ አበባ ከለውጡ ወዲህ ስሟን እና ዓለም አቀፋዊ የዲፕሎማሲ ማዕከልነቷን የሚመጥን ገጽታ ለማላበስ እና የነዋሪዎቿን ህይወት ለማሻሻል በርካታ ተግባራት የተከናወኑ ሲሆን በዚህም የሚታዩ ለውጦች ተመዝግበዋል።

በዚህም መዲናዋ ውብ፣ ጽዱ እና የዓለም አቀፍ ቱሪስቶች የስህበት ማዕከል እየሆነች መጥታለች፡፡

በተለይ በሁለት ምዕራፍ ተከፋፍሎ የተከናወነው እና በመከናወን ላይ ያለው የኮሪደር ልማት ለከተማዋ ገጽታ እና ለነዋሪዎች ህይወት መሻሻል ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክቷል፡፡

ኢዜአ በኮሪደር ልማቱ ከከተማዋ የተለያዩ ሰፈሮች ተነስተው በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ በሚገኘው አዲስ እና ደረጃውን የጠበቀ የመኖሪያ አካባቢ ህይወት መምራት የጀመሩ የህብረተሰብ ክፍሎችን አነጋግሯል።

ከፒያሳ በመልሶ ማልማት የተነሱት አልማዝ ዳምጠው፤ ቀደም ሲል በተጎሳቆለና ለህይወት ፈታኝ በሆነ አኗኗር ውስጥ ያሳልፉ እንደነበር አውስተዋል።

የኮሪደር ልማቱ መምጣቱን ተከትሎ መኖሪያ አካባቢያቸው ወደ መልሶ ማልማት ሲገባ፥ እነሱም ምቹ ካልሆነው አሮጌ አካባቢ ወጥተው ደረጃውን ወደጠበቀ የመኖሪያ መንደር መግባታቸውን ተናግረዋል፡፡

ልማቱ ከነበርንበት ደሳሳ ጎጆ በመውጣት በተሻለ ሁኔታ እንድንኖርና ልጆቻችን በምቹ ትምህርት ቤቶች እንዲማሩ ያስቻለ ነው ብለዋል፡፡

ከቄራ በመልሶ ማልማት የተነሱት ሙና ሸሪፍ በበኩላቸው፤ አሁን ያሉበት አካባቢ በውሃ፣ በጤና፣ በመብራትና ሌሎች አቅርቦቶች ከበፊቱ እጅግ የተሻለ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ትምህርት ቤቶቹ የስፖርት ማዘውተሪያ ያላቸው፣ የመመገቢያ ማዕከል የተገነባላቸው እና ደረጃቸውን የጠበቁ መሆናቸውንም አንስተዋል፡፡

የተገነቡ መሰረተ ልማቶች ዓለም አቀፍ ደረጃን ያሟሉ በመሆናቸው መንግስትን እናመሰግናለን ያሉት ደግሞ ሌላኛዋ አስተያየት ሰጪ ሰናይት ገብሩ ናቸው፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.