የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

በምስራቅ ወለጋ ዞን በሰፈነው ሰላም የልማት ሥራዎችን በፍጥነትና በጥራት ለማከናወን ተችሏል-የዞኑ አስተዳደር

Jul 10, 2025

IDOPRESS

ነቀምቴ፤ ሐምሌ 2/2017(ኢዜአ)፦በምስራቅ ወለጋ ዞን በሰፈነው ሰላም የልማት ሥራዎችን በፍጥነትና በጥራት ለማከናወን መቻሉን የዞኑ አስተዳዳሪ አቶ ወጋሪ ነገራ ገለጹ።

በዞኑ ሲቡ ስሬ ወረዳ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ማዕከል አድርገው የተገነቡ 41 የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ተመርቀው ለአገልግሎት ክፍት ሆነዋል።

የምስራቅ ወለጋ ዞን አስተዳደሪ አቶ ወጋሪ ነገራ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት በዞኑ የሰፈነው ሰላም የልማት ሥራዎችን በስፋት ለማከናወን እድል ፈጥሯል።


በተጠናቀቀው በጀት ዓመትም የዞኑን ህዝብ ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ተገንብተው ለአገልግሎት እየበቁ መሆኑን ገልጸዋል።

በዞኑ ሲቡ ሲሬ ወረዳ በ435 ሚሊዮን ብር የተገነቡ 41 የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶችም የዚሁ ጥረት አካል መሆናቸውን ተናግረዋል።

ለአገልግሎት እየበቁ ያሉ የመሰረተ ልማት ተቋማት የትምህርት፣ የጤና፣ መሰረተ ልማት እና የንጹህ መጠጥ ውሃ አቅርቦትን የሚያሳድጉ ናቸው ብለዋል።

በዞኑ ሁሉንም ነዋሪዎች ተጠቃሚ የሚያደርጉ የልማት ሥራዎች እንደሚጠናከሩ ገልጸው፣ የዞኑ ህዝብም የአካባቢውን ሰላም መጠበቅ እንዳለበት አሳስበዋል።

‎የሲቡ ስሬ ወረዳ አስተዳደሪ አቶ ጨነቀ ቡሻ በበኩላቸው ለአገልግሎት የበቁ የመሰረተ ልማት ተቋማት በመንግሥት በጀትና በህዝብ ተሳትፎ የተገነቡ ናቸው ብለዋል።


የፕሮጀክቶቹ ለአገልግሎት መብቃት ለዓመታት ሲነሱ ለነበሩ የህብረተሰብ ጥያቄዎች ምላሽ የሰጡ መሆናቸውን ገልጸው በቀጣይም የወረዳውን ነዋሪዎች ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የልማት ሥራዎች ይጠናከራሉ ብለዋል።


በመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶቹ ምርቃት ላይ የተገኙት የወረዳው ነዋሪዎችም የልማት ሥራው ተጠቃሚነታቸውን የሚያሳድግ መሆኑን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ባለፉት 10 ወራት ከወጪ ንግድ 8 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ተገኝቷል

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ባለፉት 10 ወራት ከወጪ ንግድ 8 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ማግኘት መቻሉን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁ...

May 15, 2026

ረቂቅ አዋጁ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ ይኖረዋል

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...

Apr 23, 2026

ኢትዮጵያ እና አይኤምኤፍ በኢኮኖሚው መስክ ትብብራቸውን ያጠናክራሉ

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...

Apr 17, 2026

በጀጎል ግንብ ውስጥ የሚገነባው የ”ዳር ሀረር” የመልሶ ማልማት ፕሮጀክት ግንባታ ሊጀመር ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...

Apr 12, 2026