የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

ጃይካ በኢትዮጵያ እያደረገ ያለውን የልማት ትብብር አጠናክሮ ይቀጥላል

Jul 1, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 23/2017(ኢዜአ)፦ የጃፓን ዓለም አቀፍ ትብብር ኤጀንሲ(ጃይካ) በኢትዮጵያ እያደረገ ያለውን የልማት ትብብር አጠናክሮ እንደሚቀጥል በኢትዮጵያ የጃይካ ተወካይ ኬንሱኬ ኦሺማ ገለፁ።

ጃይካ ከኢትዮጵያ ጋር ለዘመናት የዘለቀ የልማት ትብብር እንዳለው ለኢዜአ የገለጹት ተወካዩ፥ በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ስራዎች በርካታ ለውጦችን እንዳመጡ መመልከታቸውን ጠቅሰዋል።

ጃይካ በግብርናና ገጠር ልማት፣ በመሰረተ ልማት፣ ኢንዱስትሪያላይዜሽንና በትምህርት ከኢትዮጵያ ጋር በትብብር እየሰራ ይገኛል ብለዋል።

የገበያ ተኮር ግብርና፣ የሩዝ ምርታማነትና የውሃ ዘርፍ ልማትም ጃይካ ከኢትዮጵያ ጋር በትብብር ከሚሰራባቸው የትብብር መስኮች መሆናቸውንም ጠቁመዋል።

ጃይካ የአቅም ግንባታ ስልጠናዎችና ሌሎች ዘርፎች ላይ በትብብር እየሰራ መሆኑንና እያደረገ ያለውን የልማት ትብብር አጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል።

በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ስራዎች ለውጥ እያስመዘገቡ መሆኑን መመልከታቸውን ጠቅሰው፥ በአዲስ አበባ እና በሌሎች ከተሞች የተከናወኑ የልማት ስራዎች የስኬት ማሳያ መሆናቸውን ገልጸዋል።

በመላ ሀገሪቱ መሰል የልማት ስራዎችን ለማጠናከር እየተሰራ ያለውን ስራ ጃይካ እንደሚደግፍም ተወካዩ አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ባለፉት 10 ወራት ከወጪ ንግድ 8 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ተገኝቷል

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ባለፉት 10 ወራት ከወጪ ንግድ 8 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ማግኘት መቻሉን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁ...

May 15, 2026

ረቂቅ አዋጁ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ ይኖረዋል

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...

Apr 23, 2026

ኢትዮጵያ እና አይኤምኤፍ በኢኮኖሚው መስክ ትብብራቸውን ያጠናክራሉ

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...

Apr 17, 2026

በጀጎል ግንብ ውስጥ የሚገነባው የ”ዳር ሀረር” የመልሶ ማልማት ፕሮጀክት ግንባታ ሊጀመር ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...

Apr 12, 2026