የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

በፋይናንስና የግዢ ሕጎች አፈፃፀም ላይ የሚስተዋሉ ክፍተቶችን ለማስወገድ የተጀመሩ ተግባራትን ማጠናከር ይገባል

Jun 13, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 5/2017 (ኢዜአ)፦የፋይናንስና የግዢ ሕጎች አፈፃፀም ላይ የሚስተዋሉ ክፍተቶችን በሳይንሳዊ ጥናት ለማስወገድ የተጀመሩ ተግባራትን ማጠናከር ይገባል ሲሉ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ወጪ አስተዳደርና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ የሺመቤት ደምሴ(ዶ/ር) ተናገሩ።

የፍትህ ሚኒስቴር ባጠናው የፌዴራል የፋይናንስና የግዢ ሕጎች የአፈፃፀም ክፍተት መንስኤዎችና ሊወሰድ ስለሚገባው እርምጃዎችን የሚጠቁም የዳሰሳ ጥናት ማዳበሪያ መድረክ ተካሂዷል።

በውይይቱ የመንግስት ወጪ አስተዳደርና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ የሺመቤት ደምሴ(ዶ/ር)፣ የፍትህ ሚኒስትር ዴኤታ በላይሁን ይርጋ፣ የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር መሰረት መስቀሌ፣ የፌደራል ዋና ኦዲተር ምክትል ዋና ኦዲተር አቶ አበራ ታደሰ እና የሚመለከታቸው ተቋማት አመራሮች ተገኝተዋል።

የዳሰሳ ጥናቱ የፌዴራል መንግስት መስሪያ ቤቶችን የ2013 እና 2014 በጀት ዓመት የዋና ኦዲተር የፋይናንስ ኦዲት ሪፖርት መስረት አድርጎ የተከናወነ ነው።

ጥናቱ በአራት ጉዳዮች ላይ ትኩረት ያደረገ ሲሆን ሕግን ያልተከተሉ ወይም የክፍያ መስፈርቶች ሳይሟሉ የሚፈጸም ክፍያ፣ ውዝፍ ተሰብሳቢ ሂሳብ በተመለከተ፣ ተከፋይ ሂሳቦች በሚመለከለት እና የግዥ ሂደት አለመከተል ላይ ማተኩሩ ተጠቅሷል።

የመንግስት ወጪ አስተዳደርና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ የሺመቤት ደምሴ(ዶ/ር) በዚሁ ጊዜ እንዳሉት፤ የፍትህ ሚኒስቴር የፌዴራል የፋይናንስና የግዢ ሕጎች የአፈፃፀም ላይ የሚስተዋሉ ጥሰቶችን ለመለየት ያጠናው ጥናት አበረታች ነው።

ጥናቱ በአሰራሮች ላይ ያሉ ክፍተቶችን በመለየት የፋይናንስና የግዢ ሕጎችን በአግባቡ ተግባራዊ ለማድረግ ያግዛል ብለዋል።

በዚህም በባለድርሻ አካላት የተሰጡ ግብዓቶችን በማካተት አሁን ካለበት የበለጠ አዳብሮ ወደ ሥራ ማስገባት እንደሚገባ አቅጣጫ አስቀምጠዋል።

በቀጣይም በነዚህ ዘርፎች የሚስተዋሉ ከፍተቶችን በሳይንሳዊ ጥናት ለማስወገድ የተጀመሩ ተግባራትን ማጠናከር እንደሚገባ ገልጸዋል።

የፍትህ ሚኒስትር ዴኤታ በላይሁን ይርጋ በበኩላቸው ጥናቱ የተደረገው የፋይናንስና የግዢ ሕጎችን መተግበር የመንግስት ሀብት ወይም በጀት ከብክነት እና ከጥፋት ለመከላለከል ነው ብለዋል።

ሕጎችን ባግባቡ ተግባራዊ በማድረግ የሀብት አሰባሰብና የወጪ አስተዳደርን በአግባቡ በመምራት የመንግስትን የልማት ስራዎች እንዲያግዙ ለማስቻል የተደረገ እንደሆነ ተናግረዋል።

ጥናቱ ከዚህ መድረክ የተገኙ ምክረ ሃሳቦችን በማካተት የበለጠ ዳብሮ ተግባራዊ እንደሚደረግም ገልፀዋል።

የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር መሰረት መስቀሌ ጥናቱ በቀጣይ የተከናወኑ የለውጥ ስራዎችን ማካተት እንዳለበት ተናግረዋል።

የፌደራል ዋና ኦዲተር ምክትል ዋና ኦዲተር አቶ አበራ ታደሰ በበኩላቸው ጥናቱ መንስኤዎችን ለመለየትና ተጠያቂነትን ለማስፈን ጠቀሜታው የጎላ መሆኑን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ባለፉት 10 ወራት ከወጪ ንግድ 8 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ተገኝቷል

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ባለፉት 10 ወራት ከወጪ ንግድ 8 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ማግኘት መቻሉን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁ...

May 15, 2026

ረቂቅ አዋጁ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ ይኖረዋል

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...

Apr 23, 2026

ኢትዮጵያ እና አይኤምኤፍ በኢኮኖሚው መስክ ትብብራቸውን ያጠናክራሉ

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...

Apr 17, 2026

በጀጎል ግንብ ውስጥ የሚገነባው የ”ዳር ሀረር” የመልሶ ማልማት ፕሮጀክት ግንባታ ሊጀመር ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...

Apr 12, 2026