አዲስ አበባ፤ ግንቦት 28/2017(ኢዜአ)፦ስሎቪንያ በኢትዮጵያ ዘመናዊ የንብ ማነብ ስራን ለማጠናከር የባለሙያና የቴክኖሎጂ ድጋፍ እንደምታደርግ የስሎቪኒያ ሪፐብሊክ ፕሬዚዳንት ናታሳ ፒርክ ሙሳር (ዶ/ር) ገለጹ።
አገሪቱ በዘመናዊ ንብ ማነብ ላይ ያላትን ልምድ ለኢትዮጵያ በማጋራት ከዘርፉ የበለጠ ተጠቃሚ ለማድረግ ትሰራለችም ብለዋል።
በዚሁ ወቅት ዘመናዊ የንብ ማነብ ሰርቶ ማሳያ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር የተካሄደ ሲሆን በዚህም የስሎቪኒያ ሪፐብሊክ ፕሬዚዳንት ናታሳ ፒርክ ሙሳር (ዶ/ር) እና ልዑካቸው፣ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ እንዲሁም የከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
የስሎቪኒያ ሪፐብሊክ ፕሬዚዳንት ናታሳ ፒርክ ሙሳር (ዶ/ር) እንዳሉት ስሎቪንያና ኢትዮጵያ መልካም የዲፕሎማሲ ግንኙነት ያላቸው አገራት ናቸው።
ስሎቪንያ በዘመናዊ ንብ ማነብ ልምድ ያላት አገር መሆኗንና በኢትዮጵያ ለዘርፉ የባለሙያና ቴክኖሎጂ ድጋፍ እንደምታደርግ አስታውቀዋል።
ዘመናዊ የንብ ማነብ ሰርቶ ማሳያ ማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ የዛሬ ብቻ ሳይሆን ለትውልድ የሚሻገር ፕሮጀክት ነው ብለዋል።
ከዚህ ባለፈ በሌሎች መስኮችም ያለው ትብብር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል።
የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በበኩላቸው የንብ ማነብና ከተማ ግብርና ስራ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥና አካባቢን ለመጠበቅ ጠቀሜታ እንዳለው ተናግረዋል።
ብዝሃ ህይወትን ለመጠበቅና የምግብ ሉዓላዊነት የማረጋገጥ ስራ ከአየር ንብረት ለውጥ ስትራቴጂ ጋር የተሰናሰለ መሆኑንም ጠቅሰዋል።
አዲስ አበባ የጋራ የልማት ግብ ካላቸው ጋር በትብብር እንደምትሰራም ገልጸዋል።
በአዲስ ዙ ፓርክ በይፋ የተጀመረው ዘመናዊ የንብ ማነብ ሰርቶ ማሳያ የአለም አቀፍ ትብብር ማሳያ ጭምር መሆኑን ጠቅሰው፤ ለትምህርትና ለቱሪዝም ዘርፍም ጠቃሚ ነው ብለዋል።
አዲስ አበባ ፤የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፦የኢትዮ-ጅቡቲ የባቡር ትራንስፖርት ተገልጋዮች ፋይዳ መታወቂያን ተጠቅመው በዲጂታል አማራጭ ትኬት የሚቆርጡበት አሰራር ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ ጥር 03/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለስልጣን የለማ የትራንስፖርት ኦፕሬተሮችንና የጭነት ባለቤቶችን የሚገናኝ መተግበሪያ አስጀምሯል። ...
Feb 12, 2025