ሠመራ፤ ግንቦት 21/2017 (ኢዜአ)፡-በአፋር ክልል የተቀየሱ የልማት ግቦችን ለማሳካት በሚደረገው ጥረት የንግዱ ማህበረሰብ የላቀ ሚናውን እንዲያጠናክር የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ አሳሰቡ።
"ለሁለንተናዊ ብልፅግና የንግዱ ማህበረሰብ ሚና" በሚል መሪ ሀሳብ ከወረዳ ጀምሮ ሲካሄድ የቆየው የንግዱ ማህበረሰብ አባላት የማጠቃለያ መድረክ ከክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጋር ዛሬ ውይይት ተካሂዷል።
የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ በውይይት መድረኩ ላይ እንደገለጹት በክልል ደረጃ የተጀመረውን የልማት ጉዞ ዕውን ለማድረግ የንግዱ ማህበረሰብ ሚና የላቀ ነው።
ለተግባራዊነቱም የንግዱ ማህበረሰብ ግብሩን በወቅቱ የመክፈል ግዴታውን መወጣት እንዳለበት ጠቅሰው፣ የንግድ ስርአቱን በማዘመን ሂደት ከአሰራር ጋር በተያያዘ የሚነሱ ጥያቄዎችን ለመመለስ የክልሉ መንግስት በትኩረት እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
የንግዱ ማህበረሰብ ህጋዊነትን ተላብሶ የግብይት ስርአቱን ማሳለጥ እንዳለበት የተናገሩት ደግሞ የክልሉ ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ኀላፊ አቶ አህመድ አብዱልቃድር ናቸው።
ቢሮው ለንግድ ሥርአቱ ማነቆ የሆኑ አሰራሮችን ደረጃ በደረጃ እየፈታ መሆኑንም አመልክተዋል።
የክልሉ ገቢዎች ቢሮ ኀላፊ አቶ አወል አብዱ በበኩላቸው የንግዱን ማህበረሰብ ጥያቄዎች ለመመለስ እስከ ታች ድረስ በመውረድ እየተሰራ ነው ብለዋል።
ነጋዴው ገቢውን በማሳወቅና ግብሩን በወቅቱ በመክፈል የዜግነት ግዴታውን መወጣት እንዳለበትም አስገንዝበዋል።
የሠመራ ሎጊያ ከተማ አስተዳደር የንግድና ዘርፍ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ዘነበች አብርሃ በበኩላቸው "መንግስት የሚገባውን ገቢ በትክክል እንዲያገኝ በከተማ አስተዳደሩ ፈጣንና አስተማማኝ የግብር አሰባሰብ ስርአት ሊጠናከር ይገባል" ብለዋል።
በነጋዴው ማህበረሰብ የሚነሱና ከግብር ጋር የተያያዙ ጥያቄዎች በአፋጣኝ ምላሽ አግኝተው ነጋዴው ለሀገር እድገት የሚያበረክተውን ድርሻ ማጉላት እንደሚገባም አስረድተዋል።
የአፋር ክልል ንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት ቦርድ አባል አቶ ከበደ መሐመድ በበኩላቸው፣ ህገ ወጥ ንግድን ለመከላከልና የመንግስት ገቢ ባግባቡ ለመሰብሰብ የንግዱን ማህበረሰብ ማወያየት ወሳኝ መሆኑን ጠቅስዋል።
ከዚህ ባለፈ የንግድ ሥርአቱን ለማዘመን የሚያስችሉ የአሰራርና የህግ ማዕቀፎች መሻሻል እንዳለባቸው ጠቁመዋል።
በውይይት መድረኩ ላይ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮችና የሠመራ ሎጊያ ከተማ አስተዳደር የንግዱ ማህበረሰብ አባላት ተገኝተዋል።
አዲስ አበባ ፤የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፦የኢትዮ-ጅቡቲ የባቡር ትራንስፖርት ተገልጋዮች ፋይዳ መታወቂያን ተጠቅመው በዲጂታል አማራጭ ትኬት የሚቆርጡበት አሰራር ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ ጥር 03/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለስልጣን የለማ የትራንስፖርት ኦፕሬተሮችንና የጭነት ባለቤቶችን የሚገናኝ መተግበሪያ አስጀምሯል። ...
Feb 12, 2025