የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

በጋምቤላ ክልል የመኸር እርሻ ልማቱን በማጠናከር የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ እየተሰራ ነው - ርዕሰ መስተዳድር ዓለሚቱ ኡሞድ

May 30, 2025

IDOPRESS

ጋምቤላ፤ ግንቦት 21/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል የመኸር እርሻ ልማቱን በማጠናከር የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥና የታለመውን ግብ ለማሳካት በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ዓለሚቱ ኡሞድ ገለጹ።

ርዕሰ መስተዳድሯ ከፌዴራልና ከክልሉ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ጋር በመሆን በአኝዋሃ ዞን አቦቦ ወረዳ እየተከናወነ ያለውን የመኸር እርሻ ተዘዋውረው ተመልክተዋል።

ርዕሰ መስተዳድሯ በጉብኝቱ ወቅት ለኢዜአ እንደገለጹት በዘንድሮው የመኸር እርሻ ልማት የተጠናከረ የህዝብ ንቅናቄ በመፍጠር መሬት ጦሙን እንዳያድር በትኩረት እየተሰራ ነው።


በዘንድሮው የመኸር እርሻ ከመቼውም ጊዜ በተሻለ የምርት ማሳደጊያ ግብዓቶችን ለአርሶና አርብቶ አደሩ በማቅረብ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በትጋት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

በተለይም አርሶና አርብቶ አደሩን በማደራጀት፣ የኩታ ገጠም ግብርና ልማት ስራዎችን በማስፋት፣ ምርታማነትን ለማሳደግ የተጀመረውን ጥረት በማጠናከርና የምግብ ሉዓላዊነትን የማረጋገጡ ተግባር ተጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል ብለዋል።

በዕለቱ በአርሶና አርብቶ አደሩ ማሳ ላይ የተመለከቱት የመኸር እርሻ ልማት እንቅስቃሴ አበረታችና ተስፋ ሰጪ መሆኑንም ገልጸዋል።

በመስክ ምልከታው የነበሩት የግብርና ሚኒስትሩ አማካሪ ታረቀኝ ጽጌ በዚሁ ወቅት እንዳሉት በክልሉ የግብርና ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የህዝቡን ኑሮ ለመለወጥና በምግብ ራስን ለመቻል እየተከናወነ ያለው ስራ የሚበረታታ መሆኑን ተመልክተናል ብለዋል፡፡


በተለይም አርሶ አደሩ በኩታ ገጠም እርሻ በመደራጀት እያከናወነ ያለው የግብርና ልማት ምርታማነትን ማሳደግ የሚያስችል በመሆኑ መጠናከር ያለበት መሆኑን አክለዋል፡፡

አርሶ አደሩ ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችን ለመጠቀም ያለው ፍላጎት ከፍተኛ መሆኑን በመስክ ምልከታው መረዳታቸውን ጠቅሰው ሚኒስቴሩ አርሶ አደሮቹ የሚያነሱትን የግብዓት ክፍተት ለመሙላት በትኩረት ይሰራል ነው ያሉት፡፡

አርሶ አደር እስማኤል ሁሴን በሰጡት አስተያየት መንግስት አርሶ አደሩን በኩታ ገጠም እርሻ አደራጅቶ ወደ ልማት ካስገባ ወዲህ ተጠቃሚ እየሆንን ነው ብለዋል፡፡


ዘንድሮ መንግስት የእርሻ ትራክተርና ምርጥ ዘር በወቅቱ ስላቀረበ ካለፈው ጊዜ በተሻለ ማሳቸውን በዘር መሸፈናቸውን የተናገሩት ደግሞ አርሶ አደር አጉዋ ካን ናቸው፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.