የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

መንግስት ለአምራች ኢንዱስትሪው የሰጠው ትኩረት ዘርፉ እንዲነቃቃ አድርጎታል

May 28, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 19/2017(ኢዜአ)፦ መንግስት ለአምራች ኢንዱስትሪው በሰጠው ትኩረት አሁን ላይ ዘርፉ እየተነቃቃ መሆኑን የኢንዱስትሪ ሚኒስትር ዴኤታ ታረቀኝ ቡሉልታ ገለፁ።

የአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፉ የኢትዮጵያን ብልፅግና ለማረጋገጥና መዋቅራዊ ሽግግርን ለማምጣት ወሳኝ መሆኑንም ገልጸዋል።

ሚኒስትር ዴኤታው ለኢዜአ እንዳሉት በዘርፉ የአሰራር ስርዓት ማሻሻያዎችና እንደ በአፍሪካና በቀጣናው ተወዳዳሪ የሚያደርግ አዲስ የኢንዱስትሪ ፖሊሲ ተዘጋጅቷል።

ማሻሻያውን ተከትሎ አምራች ኢንዱስትሪ ዘርፉ የነበረበት የውጭ ምንዛሬ ችግር እንዲፈታ ያስቻለ መሆኑን ገልፀዋል።

ከፌዴራል እስከ ክልልና ከተማ አስተዳደር እየተካሄደ ያለው የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የህብረተሰቡን ግንዛቤ የማሻሻልና የአምራች ኢንደስትሪ ዘርፍ ችግሮች በቅንጅት እንዲፈቱ እያደረገ መሆኑን ጠቁመዋል።

ንቅናቄው ተዘግተው የነበሩ ኢንዱስትሪዎች ወደ ስራ እንዲገቡ፣ የኢንዱስትሪዎች የማምረት አቅም እንዲሻሻል፣ የገበያ እድል ለመፍጠርና አዳዲስ ኢንቨስትመንትን ለመሳብ አስተዋፅኦ ማበርከቱን ገልፀዋል።

ባለፉት ሶስት አመታት የኢንዱስትሪዎች የማምረት አቅም ከ46 በመቶ ወደ 61 ነጥብ 2 በመቶ ማደጉንም ነው ያስረዱት።

ተኪ የኢንዱስትሪ ምርቶች ላይ ውጤታማ ተግባራት መከናወናቸውንና ባለፉት ዘጠኝ ወራትም 3 ነጥብ 1 ቢሊዮን ዶላር በአገር ውስጥ መተካት መቻሉን ገልጸዋል።

የአገር ውስጥ የገበያ ድርሻ ከነበረበት 30 በመቶ ወደ 44 በመቶ ማደግ መቻሉንም ነው የተናገሩት።

የአገሪቱን እድገት ቀጣይነት ያለው፣ ተወዳዳሪና አስተማማኝ ለማድረግ የአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፉ ወሳኝ ነው ብለዋል።

ለዚህም በዘርፉ ያለውን ኢንቨስትመንት ማሳደግ እንደሚጠበቅ ተናግረው፤ የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራትን ማሻሻል ኢንቨስትመንትን ለማሳደግ ያስፈልጋል ነው ያሉት።

መንግስት ለአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ በሰጠው ትኩረት አሁን ላይ ዘርፉ እየተነቃቃ መሆኑን አብራርተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ባለፉት 10 ወራት ከወጪ ንግድ 8 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ተገኝቷል

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ባለፉት 10 ወራት ከወጪ ንግድ 8 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ማግኘት መቻሉን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁ...

May 15, 2026

ረቂቅ አዋጁ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ ይኖረዋል

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...

Apr 23, 2026

ኢትዮጵያ እና አይኤምኤፍ በኢኮኖሚው መስክ ትብብራቸውን ያጠናክራሉ

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...

Apr 17, 2026

በጀጎል ግንብ ውስጥ የሚገነባው የ”ዳር ሀረር” የመልሶ ማልማት ፕሮጀክት ግንባታ ሊጀመር ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...

Apr 12, 2026