የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

በድሬዳዋ የልማት ፕሮጀክቶች ኢኮኖሚን የሚያነቃቁና በአርአያነት የሚጠቀሱ ናቸው

May 21, 2025

IDOPRESS

ድሬዳዋ፤ ግንቦት 11/2017(ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ፕሮጀክቶች ኢኮኖሚን የሚያነቃቁና በአርአያነት የሚጠቀሱ መሆናቸውን የብልፅግና ፓርቲ የህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ኃላፊ ቢቂላ ሁሪሳ(ዶ/ር) ተናገሩ።

ሀላፊው በድሬዳዋ አስተዳደር በግንባታ ላይ የሚገኙ የኮሪደር ልማት፣ የማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ማምረቻ ሼዶች፣ የኮንቬንሽን ማዕከል እና በመደመር መፅሐፍ ሽያጭ ግንባታው በመጠናቀቅ ላይ ያለውን ዘመናዊ ቤተ መጻህፍት ተመልክተዋል።

በአስተዳደሩ የተመለከቷቸው የልማት ፕሮጀክቶች የድሬዳዋን ኢኮኖሚ በማነቃቃት የህዝብን ተጠቃሚነት እንደሚያረጋግጡ ገልጸው፣ በአርአያነት የሚጠቀሱ መሆናቸውንም ተናግረዋል።

በድሬዳዋ የለውጡ አመራር የጋራ ህብረትና መደጋገፍ እንዲሁም የነዋሪው የተቀናጀ ተሳትፎ እየተመዘገቡ ለሚገኙ አበረታች ውጤቶች መሰረታዊ አስተዋጽኦ ማድረጋቸውንም ገልጸዋል።

ከልማቱ በተጨማሪ በድሬዳዋ እየተፈጠረ ያለው የጋራ ገዢ ትርክትና ሕብረ ብሔራዊ አንድነት በአርአያነት የሚጠቀስ መሆኑንም ተናግረዋል።

በድሬዳዋ በተለያዩ መስኮች እየተመዘገቡ ያሉ ውጤቶች ይበልጥ ሲጠናከሩ የነዋሪዎችን ተጠቃሚነት ያሳድጉታልም ነው ያሉት።

በልማት ሥራዎች ጉብኝት ላይ የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሃርን ጨምሮ የአስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች ተሳትፈዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.