
አዲስ አበባ፤ግንባት 7/2017 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ በአጭር ጊዜ ውስጥ አመርቂ ስኬት ማስመዝገቡን የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ ገለጹ።
ለሁለት ቀናት የሚቆየው የኢትዮጵያ ፋይናንስ ፎረም በአዲስ አበባ ሳይንስ ሙዚየም መካሄድ ጀምሯል።
በፎረሙ ላይ ከፍተኛ የመንግስት አመራሮች፣የሀገር ውስጥና የዓለም አቀፍ የባንክ የስራ ኃላፊዎች፣ የዓለም አቀፍ የገንዘብና የልማት አጋር ተቋማት ተወካዮች ተገኝተዋል።
የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀ ሥላሴ፥ ከአንድ ክፍለ ዘመን በላይ ዕድሜ ያለው የኢትዮጵያ የፋይናንስ ኢንዱስትሪ የሚፈለገውን ያህል ዕድገት ሳያስመዘግብ መቆየቱን አውስተዋል።
በኢትዮጵያ የፋይናንስ ኢንዱስትሪ የነበሩ መሰናክሎችን ለማለፍም አካታችና ዘመኑን የዋጀ ሥርዓት የሚፈጥር የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ተግባራዊ መደረጉን ተናግረዋል።
የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ተግባራዊ በተደረገ በአጭር ጊዜ ውስጥ አመርቂ ውጤት መመዝገቡን ገልጸዋል።
በቀጣይም የኢትዮጵያን የፋይናንስ ኢንዱስትሪ ወደ ዲጂታል ሥርዓት ለማሸጋገር ቀጣይነት ያለው ስራ እንደሚጠይቅ አስገንዝበዋል።
የኢትዮጵያ የፋይናንስ ፎረም ለዘርፉ አንገብጋቢ ችግሮች ምላሽና መፍትሔ አመላካች ምክረ ሃሳቦችን በመስጠት የግሉን ዘርፍ ለማነቃቃት ጉልህ ፋይዳ እንደሚኖረው አስረድተዋል።
የብሔራዊ ባንክ ገዥ ማሞ ምህረቱ በበኩላቸው፥ የኢትዮጵያ ማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ዓለም አቀፍ ድጋፍና ዕውቅና ማግኘቱን ጠቁመዋል።
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ባለፉት 10 ወራት ከወጪ ንግድ 8 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ማግኘት መቻሉን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁ...
May 15, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...
Apr 23, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...
Apr 17, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...
Apr 12, 2026