ባህርዳር፤ግንቦት 4/2017(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል የተገኘውን ሰላም በማፅናት በሁሉም ዘርፍ ተጨባጭ ውጤት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕስ መስተዳደር አቶ አረጋ ከበደ ገለጹ።
የክልሉ የመንግስት አመራር አባላት በወቅታዊ የሰላም ጉዳይ ላይ በባርዳር ከተማ የውይይት መድረክ እያካሄዱ ነው።
ዛሬ በተጀመረው የውይይት መድረኩ ላይ ርዕሰ መስተዳድር አቶ አረጋ ከበደ እንዳመለከቱት፤ በክልሉ የተከናወነው የህግ የበላይነት የማስከበር ተግባር ውጤታማ ነው።
በዚህም ሰላምን በማፅናት በሁሉም ዘርፍ ተጨባጭ ውጤት ማስመዝገብ መቻሉን ገልጸው፤ ይህም መሰረተ ልማትን በመገንባት፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተግባራትን በማከናወን እንደሆነ አስታውቀዋል።
በቀጣይም የህዝብን የልማት ተጠቃሚነት ይበልጥ ለማሳደግ በየደረጃው ያሉ አመራር አባላት እስካሁን ሲያከናውኑ ከቆዩት በላቀ ደረጃ በቁርጠኝነት መትጋት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል።
በብልፅግና ፓርቲ የአማራ ክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ይርጋ ሲሳይ በበኩላቸው፤ ፅንፈኛውን ቡድን ከክልሉ በማፅዳት ልማትን በዘላቂነት የማስቀጠሉ ተግባር መጠናከሩን ተናግረዋል።
በክልሉ የፀናውን ሰላም በማስቀጠል የሕዝቡን የልማት ተጠቃሚነቱን ይበልጥ ለማጎልበት በየደረጃው ያለው አመራር አበክሮ መስራት እንዳለበት አሳሰበዋል።
በውይይት መድረኩ በየደረጃው ያሉ አመራር አባላት እየተሳተፉ ነው።
አዲስ አበባ ፤የካቲት 15/2017(ኢዜአ)፦የኢትዮ-ጅቡቲ የባቡር ትራንስፖርት ተገልጋዮች ፋይዳ መታወቂያን ተጠቅመው በዲጂታል አማራጭ ትኬት የሚቆርጡበት አሰራር ...
Feb 24, 2025
አዲስ አበባ፤ ጥር 03/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለስልጣን የለማ የትራንስፖርት ኦፕሬተሮችንና የጭነት ባለቤቶችን የሚገናኝ መተግበሪያ አስጀምሯል። ...
Feb 12, 2025