
ባህር ዳር፤ ሚያዝያ 29/2017(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በማዕድን ዘርፍ 7 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር ካፒታል ላስመዘገቡ ባለሀብቶች ፈቃድ መሰጠቱን የክልሉ ማዕድን ሃብት ልማት ቢሮ አስታወቀ።
የቢሮው ኃላፊ አቶ ኃይሌ አበበ ለኢዜአ እንደገለጹት በክልሉ የማዕድን ሃብትን በአግባቡ በማጥናትና በማልማት ከዘርፉ የሚጠበቀውን ኢኮኖሚያዊ ጥቅም ለማግኘት እየተሰራ ነው።
ባለፉት ዘጠኝ ወራት በኮንስትራክሽን ማዕድን ልማት ለመሰማራት 7 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር ካፒታል በማስመዝገብ ጥያቄ ላቀረቡ 4ሺህ 326 ባለሃብቶች ፈቃድ መሰጠቱን ገልጸዋል።
በከፍተኛ፣ መካከለኛ እና አነስተኛ የኮንስትራክሽን ዘርፍና በባህላዊ ማዕድን ምርት ለተሰማሩ ባለሃብቶች ፍቃዱ መሰጠቱን ነው የተናገሩት።
ቢሮው በክልሉ ከሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች ጋር በመቀናጀት በካርታ የተደገፈ የማዕድን ክምችትና ልየታ ጥናት በተለያዩ አካባቢዎች እያካሄደ መሆኑንም አመልክተዋል።
የማዕድን ክምችት፣ አይነትና መጠንን ከመለየት ባለፈ የተገኙ ማዕድናትን በማስተዋወቅ የሀገር ውስጥና የውጭ ባለሃብቶችን በመሳብ ለማልማት እየተሰራ መሆኑን አስረድተዋል።
በዘጠኝ ወራት በተከናወኑ የማዕድን ፍለጋና ግመታ ጥናቶች ከታቀደው 80 በመቶ የሚሆነውን ማሳካት መቻሉንም ተናግረዋል።
በጥናቱ የኮንስትራክሽን፣ የኢንዱስትሪ፣ የኢነርጂ፣ ብረት ነክ እንዲሁም የከበሩና በከፊል የከበሩ ማዕድናትን በመለየት ለማዕድን ኢንቨስትመንት ምቹ የማድረግ ሥራ መሰራቱን ቢሮ ሀላፊው አስታውቀዋል።
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ባለፉት 10 ወራት ከወጪ ንግድ 8 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ማግኘት መቻሉን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁ...
May 15, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...
Apr 23, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...
Apr 17, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...
Apr 12, 2026