
ደሴ፤ ሚያዝያ 19/2017(ኢዜአ)፦ የአማራ ክልል 9ኛው የቴክኖሎጂ፣ የክህሎት፣ የተግባራዊ ጥናትና ምርምር እና የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች የንግድ ትርዒት እና የደረጃ ሽግግር ሳምንት በኮምቦልቻ ከተማ ተከፈተ።
የንግድ ትርኢትና የደረጃ ሽግግር ሳምንቱን የከፈቱት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ እና የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፋሪሃት ካሚል ናቸው።
በሥነ-ስርአቱ የአማራ ክልል ሥራና ስልጠና ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ አማረ አለሙ እንደገለፁት ፕሮግራሙ በዘርፉ የተሰማሩ ሙያተኞች የቴክኖሎጂ እውቀታቸውን ማዳበር የሚያስችል ነው።

ከዛሬ ጀምሮ ለአምስት ቀናት በሚቆየው የንግድ ትርኢትና የደረጃ ሽግግር ሳምንት 110 በክህሎት፣ 75 የቴክኖሎጂ ተወዳዳሪዎች የሚሳተፉ ሲሆን 57 የፈጠራ ሥራዎችም ለእይታ ይቀርባሉ ብለዋል።
ባለፉት ዓመታት በየተሰማሩበት የሥራ ዘርፎች ለውጥ ያመጡ 345 አነስተኛ ኢንተርፕራይዞችም ወደ ታዳጊና መካከለኛ ባለሀብትነት ይሸጋገራሉ ብለዋል።
በፕሮግራሙ ላይ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አብዱ ሁሴን(ዶ/ር)፣ አፈ-ጉባኤ ፋንቱ ተስፋዬ፣በምክትል ርእሰ መሥተዳደር ማዕረግ የከተማ ልማት ዘርፍ አስተባባሪ እና የከተሞች እና መሠረተ ልማት ቢሮ ኃላፊ አህመዲን መሀመድ (ዶ/ር) እና ሌሎች የክልሉ አመራሮች ተገኝተዋል።
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ባለፉት 10 ወራት ከወጪ ንግድ 8 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ማግኘት መቻሉን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁ...
May 15, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...
Apr 23, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...
Apr 17, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...
Apr 12, 2026