የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

በሲዳማ ክልል የቡና ችግኝ ተከላ መርሀ ግብር ተጀመረ

Apr 24, 2025

IDOPRESS

ሀዋሳ፤ ሚያዚያ 16/2017(ኢዜአ):- በሲዳማ ክልል የቡና ችግኝ ተከላ መርሀ ግብር በሸበዲኖ ወረዳ ፉራ ቀበሌ ተጀምሯል።

በማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ የክልሉ ቡና፣ ፍራፍሬና ቅመማቅመም ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ መስፍን ቃሬ እንደገለጹት፤ በክልሉ ከ29 ሚሊዮን በላይ የተሻሻለ የቡና ችግኝ ለመትከል ታቅዷል።

ሙሉ ፓኬጅን በመጠቀም ወደ ተከላ የተገባው በክልሉ የቡና ምርትና ምርታማነትን ለማጠናከር መሆኑን አመልክተዋል።


በባህር ዛፍ የተያዘ ሰፊ መሬትን ነጻ በማድረግ የቡና ልማት ላይ እንዲውል እየተደረገ መሆኑን አውስተዋል።

ይህም የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ እንደሚረዳ ገልጸዋል።

በዚህም ከባህር ዛፍ ነጻ የተደረገን ጨምሮ ከ11ሺህ ሄክታር መሬት ላይ ተከላ እንደሚከናወን አስታውቀዋል።

በማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይ የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ-ጉባኤ ፋንታዬ ከበደና ሌሎች ከፍተኛ የሥራ ሀላፊዎች ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.