የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

የልዑካን ቡድኑ የኢትዮጵያ እና ብራዚል የግብርና ትብብር ማጠናከር ያለመ ጉብኝት እያደረገ ነው

Apr 24, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 15/2017(ኢዜአ)፦ በግብርና ሚኒስትር ዴኤታ መለስ መኮንን (ዶ/ር) የተመራው ከፍተኛ የልዑካን ቡድን በብራዚል የስራ ጉብኝት እያደረገ ይገኛል።

የልዑካን ቡድኑ ከግብርና ሚኒስቴር እና ከሚኒስቴሩ ተጠሪ ተቋማት፣ ከዓለም አቀፍ የእንስሳት ምርምር ኢንስቲትዩት እና የዓለም ባንክ የተውጣጣ ነው።


ልዑኩ ከብራዚል ንግድ እና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ምክትል ፀሐፊ ማርሴል ሞሪራ ጋር ተወያይቷል።

የጉብኝቱ አላማ በግብርና ኤክስቴንሽንና ምርምር ላይ ልምድ ለመቅሰምና የሁለትዮሽ ትብብርን ማጠናከር መሆኑን የግብርና ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.