የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

ለጎንደር ከተማ የመልሶ ግንባታ የገቢ ማሰባሰቢያ መርኃ ግብር ሊካሄድ ነው

Apr 24, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ሚያዚያ 15/2017 (ኢዜአ)፦የጎንደር ከተማን ሥምና ዝና ለመመለስ እየተከናወነ ላለው የመልሶ ግንባታ ልማት "ኑ ጎንደርን እንሞሽር" በሚል መሪ ሀሳብ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐ ግብር ሊካሄድ መሆኑን የጎንደር ከተማ አስተዳደር ጥሪ አቀረበ።


የጎንደር ከተማ አሥተዳደር ከንቲባ ቻላቸው ዳኛው በሰጡት መግለጫ የገቢ ማሰባሰቢያ መርኃ ግብር ሚያዝያ 20 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ ሸራተን ሆቴል እንደሚካሄድ ተናግረዋል።


የጎንደር ከተማን የቀደመ ስምና ዝና ለመመለስ የመልሶ ግንባታ እና መሰረተ ልማትን የማሟላት ስራዎች እየተከናወኑ ነው ብለዋል።


ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የከተማዋን መልሶ ግንባታ በማስጀመር የመፍረስ አደጋ ተጋርጦባቸው የነበሩ ታሪካዊ ቅርሶች እንዲታደሱ ማድረጋቸውን ገልጸዋል።


በዚህም ለዓመታት ደብዝዞ የቆየው የጎንደር ገጽታ መፍካቱን ነው የጠቀሱት።


የልማት ሥራዎችን አጠናክሮ ለማስቀጠል ሁሉም ኢትዮጵያውያን የድርሻቸውን እንዲወጡ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባው ጥሪ አቅርበዋል።


የጎንደርን የትንሳኤ ጉዞ ማሳካት አለብን ያሉት አቶ ቻላቸው፥ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሃ ግብሩ ጎንደርን በማልማት ስራ ሁሉም የድርሻውን እንዲወጣ ያለመ መሆኑንም አንስተዋል።


በመሆኑም በሀገር ውስጥም ሆነ በመላው ዓለም የሚገኙ የጎንደር ተወላጆች፣ መላው ኢትዮጵያውያን፣ የዓለምአቀፍ ተቋማትና ኤምባሲዎች ድጋፍ እንዲያደርጉ ጠይቀዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.