የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

የክህሎት ባንኩ እንደሀገር ለተጀመረው የክህሎት ልማት መስፈንጠሪያ የሚሆን ነው - ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል

Apr 11, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 2/2017(ኢዜአ)፡- የፈጠራ ውጤቶች የክህሎት ባንክ እንደሀገር ለተጀመረው የክህሎት ልማት መስፈንጠሪያ እንደሆነ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገለፁ።

በሰመር ካምፕ እና በክህሎት ኢትዮጵያ መርኃ ግብር የተሰሩ የፈጠራ ውጤቶች የክህሎት ባንክ ትናንት ተከፍቷል።


ባንኩን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል መርቀው ከፍተውታል።

ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል በዚሁ ጊዜ እንደገለፁት፤ በባንኩ የሚገኙት የፈጠራ ውጤቶች በባለፈው ዓመት የሰመር ካምፕ ፕሮግራም እንዲሁም በዘንድሮ የክህሎት ኢትዮጵያ ተሳታፊዎች የተሰሩ እና እየተሰሩ ያሉ የቴክኖሎጂ ውጤቶች የሚገኝበት ነው።

የክህሎት ባንክ የቴክኖሎጂ ባለቤቶችን የፈጠራ ምርቶችን መጠቀምና ማስመረት ከሚፈልጉ ደንበኞች ጋር የሚያገናኝ መሆኑን ገልጸዋል።

ባንኩ ለጎብኚዎች ክፍት ሲሆን የመንግስት እና የግል ዘርፉ የፈጠራ ውጤቶችን በመጎብኘት እንዲመረትላቸው የሚፈልጓቸውን የቴክኖሎጂ ምርትች ትዕዛዝ መስጠት የሚችሉበት ምቹ ሁኔታ መፈጠሩንም ተናግረዋል።

ይህ ለሀገሪቱ የመጀመሪያው የሆነው የክህሎት ባንክ ለክህሎት ልማት ትልቅ መስፈንጠሪያ እንደሚሆንም ነው ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል የገለጹት።

ከዚሁ ጋር በተያያዘ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት ለ21 ኢንተርፕራይዞች ያዘጋጀው የመስሪያ ቦታ ርክክብ ተደርጓል።


የኢፌዴሪ ቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ብሩክ ከድር(ዶ/ር) ርክክብ የተደረገው የፈጠራ ሀሳብን ወደ ተግባር ለቀየሩ ስራ ፈጣሪዎች ነው ብለዋል።


የማሽነሪና በቀላሉ ድጋፍ አግኝተው ወደ ገበያ መውጣት ለሚችሉ የስራ ፈጠራዎች ርክከብ መደረጉን ነው የገለፁት።


የቦታ ርክክብ የተደረገላቸው የፈጠራ ባለቤቶች የሆኑት እሱባለሁ አለልኝ እና አህላም አሊ ድጋፉ የፈጠራ ስራቸውን በስፋት ለመስራት እንደሚያስችላቸው ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ባለፉት 10 ወራት ከወጪ ንግድ 8 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ተገኝቷል

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ባለፉት 10 ወራት ከወጪ ንግድ 8 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ማግኘት መቻሉን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁ...

May 15, 2026

ረቂቅ አዋጁ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ ይኖረዋል

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...

Apr 23, 2026

ኢትዮጵያ እና አይኤምኤፍ በኢኮኖሚው መስክ ትብብራቸውን ያጠናክራሉ

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...

Apr 17, 2026

በጀጎል ግንብ ውስጥ የሚገነባው የ”ዳር ሀረር” የመልሶ ማልማት ፕሮጀክት ግንባታ ሊጀመር ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...

Apr 12, 2026