የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

ኢትዮጵያ ለንግድና ኢንቨስትመንት መጎልበት በትኩረት እየሰራች ነው - ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር)

Mar 13, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 3/2017(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ ለንግድና ኢንቨስትመንት መጎልበት በትኩረት እየሰራች ነው ሲሉ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ(ዶ/ር) ገለጹ።

ሚኒስትሩ በኢትዮጵያ የዩናይትድ ኪንግደም ኤምባሲ የልማት ዳይሬክተር ፖል ዋልተርስ የተመራ ቡድንን በጽህፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።

የውጭ ባለሀብቶች በኢትዮጵያ በተለያዩ ዘርፎች እንዲሰማሩ ቁልፍ ማሻሻያዎች ተደርገዋል - ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር)

ኢትዮጵያ ለንግድና ኢንቨስትመንት መጎልበት በትኩረት እየሰራች መሆኗንና ከመቼውም ጊዜ በላይ አስቻይ ሁኔታ መኖሩን አስገንዝበናል ሲሉ ለልኡካን ቡድኑ መግለጻቸውን በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው አስፍረዋል፡፡


ኢትዮጵያና ዩናይትድ ኪንግደም ጠንካራ የንግድ ግንኙነት ያላቸው ሀገራት ናቸው ያሉት ሚኒስትሩ ሚስተር ፓል በበኩላቸው ዩናይትድ ኪንግደም ኢትዮጵያ እያሳየች ላለችው የኢኮኖሚ ሪፎርም ድጋፏን አጠናክራ እንደምትቀጥል አረጋግጠዋል ሲሉም ገልጸዋል።

ለአለም ንግድ ድርጅት አባልነት እያደረግን ያለውን ዝግጅትም አድንቀዋል ብለዋል።

በሁለትዮሽ የገበያ ዕድሎች ዙሪያ በቀጣይነት በጋራ በምንሰራባቸው አግባቦች ላይ ውጤታማ ውይይት አድርገናል ሲሉም ሚኒስትሩ ገልጸዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.