የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

<p>ሀብቶችን ወደ ተጨባጭ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት ለመቀየር በትኩረት ይሰራል - ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር)</p>

Mar 3, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 22/2017(ኢዜአ)፦ሀብቶችን ወደ ተጨባጭ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት ለመቀየር በትኩረት ይሰራል ሲሉ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ገለጹ።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የቀጣይ ሶስት ዓመት ዕቅድ ላይ ያተኮረ የውይይት መድረክ ተጀምሯል።


እቅዱ የክልሉን የልማት አቅምና ጸጋ መነሻ በማድረግ የተዘጋጀ መሆኑ ተገልጿል።

የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) በክልሉ ያሉ ተፈጥሯዊና ሰብአዊ ሀብቶችን ወደ ተጨባጭ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት ለመቀየር በልዩ ትኩረት እንደሚሰራ ገልጸዋል።

ለእቅዱ መሳካት ሁሉም ባለድርሻ አካላት በቁርጠኝነት እንዲሰሩም አሳስበዋል።

በመድረኩ እቅዱን አስመልክቶ በሚቀርቡ ሰነዶች ላይ ውይይት በማድረግ ቀጣይ አቅጣጫ ይቀመጣል ተብሎ እንደሚጠበቅ የክልሉ ኮሙኒኬሽን መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.