
አዲስ አበባ፤ የካቲት 22/2017(ኢዜአ)፦ሀብቶችን ወደ ተጨባጭ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት ለመቀየር በትኩረት ይሰራል ሲሉ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ-መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር) ገለጹ።
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የቀጣይ ሶስት ዓመት ዕቅድ ላይ ያተኮረ የውይይት መድረክ ተጀምሯል።

እቅዱ የክልሉን የልማት አቅምና ጸጋ መነሻ በማድረግ የተዘጋጀ መሆኑ ተገልጿል።
የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) በክልሉ ያሉ ተፈጥሯዊና ሰብአዊ ሀብቶችን ወደ ተጨባጭ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት ለመቀየር በልዩ ትኩረት እንደሚሰራ ገልጸዋል።
ለእቅዱ መሳካት ሁሉም ባለድርሻ አካላት በቁርጠኝነት እንዲሰሩም አሳስበዋል።
በመድረኩ እቅዱን አስመልክቶ በሚቀርቡ ሰነዶች ላይ ውይይት በማድረግ ቀጣይ አቅጣጫ ይቀመጣል ተብሎ እንደሚጠበቅ የክልሉ ኮሙኒኬሽን መረጃ ያመለክታል።
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፦ባለፉት 10 ወራት ከወጪ ንግድ 8 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ማግኘት መቻሉን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁ...
May 15, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-የጉምሩክ አዋጅ ረቂቅ ማሻሻያ የወጪና የገቢ ንግድን ለማሳለጥ የጎላ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በህዝብ ተወካዮች ምክር ...
Apr 23, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ዙሪያ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማጎ...
Apr 17, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 2/2018 (ኢዜአ)፦ የሀረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በጀጎል አለም አቀፍ ቅርስ ውስጥ የሚገነባው የ''ዳር ሀረር'' መልሶ ማልማት ፕሮ...
Apr 12, 2026